Translate

Tuesday, April 21, 2015

በአዲስ አበባ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው፣ ሰልፈኛው በሊቢያ የኢትዮጵያውያንን መገደልና መንግስት ያሳየውን ቸልተኛነት በመቃወም ላይ ነው

**** ሰበር ዜና፣ ሰልፈኛው የኢቲቪ/ ኢብኮ ጋዜጠኞችን ደበደበ ****

(ነገረ-ኢትዮጵያ) ከደቂቃዎች በፊት የኢቲቪ/ ኢብኮ ጋዜጠኞች በለቀስተኞች መደብደባቸው ተሰምቷል፡፡ የኢትቪ /ኢብኮ ጋዜጠኞች ለቅሶ ቤት ውስጥ ቀረጻ አድርገው ሲመለሱ ‹‹ሌቦች እናንተ ልታስተላልፉት አይደለም፡፡ ስለ እኛ ምን አገባችሁ?›› ተብለው እንደተደበደቡ ለማወቅ ተችሏል፡፡
—————————
Addis Ababa protest against Ethiopian government
በሊብያ አሸባሪዎች በኢትዮጵያውያን ላይ የፈጸሙትን አሰቃቂ ግድያ ለማውገዝና መንግስት ነኝ ባዩ ወያኔ ያሳየውን ቸልተኛነት ለመቃወም በአዲስ አበባ ህዝቡ ነቅሎ አደባባይ ወጥቷል።

ይሁንና ፖሊስ እንደተለመደው ሰልፉን ለመበተን ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፣ ነገረ-ኢትዮጵያ እንደዘገበው ከሆን ፖሊስ ሰልፈኛውን በዱላ መደብደብ ጀምሯል።
ሰልፉ ከፖሊሶቹ ቁጥጥር በላይ ሆኗል፣ በርካታ ህዝብ እየጮኸ እና እያለቀሰ ሰልፈኛውን መቀላቀሉን ቀጥሏል።
ሰልፈኞቹ ከሚያሰሙት መፈክሮች መካከል፣
‹ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት የለም!››
‹‹መንግስት የሌለው ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው!››
‹‹የወንድሞቻችን ደም በከንቱ ፈሶ አይቀርም!››
‹‹የወንድሞቻችን ደም ውሃ አይደለም!››
ሰልፈኛው በተለይ ወጣቱ በቁጭት ለሟቾቹ ትኩረት ያልሰጠው መንግስት ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰማ ነው!
‹‹ሌባ! ሌባ!ሌባ! ሌባ!ሌባ! ሌባ!››
ሰልፉ ቀጥሏል፣ ፖሊስ ሰዎች ሰልፈኛውን እንዳይቀላቀሉ ጥረት እያደረገ ነው።
Porotest in Addis Ababa, against ISIS and Ethiopian government
protest in Addis Ababa

No comments:

Post a Comment