Translate

Friday, March 6, 2015

ተዋቂው ጋዜጠኛ አለምንህ ዋሴ የህዝቡን ትግል ተቀላቀለ !

 

2_1812ጋዜጠኛው በኢትዮጵያዊነቱ አያሌ በደሎች እንደ ተፈጸሙበት ያወጋል ! በተለይ ይላል ጋዚጠኛ አለምነህ ዋሴ ፍትህ እኩልነት በሌለባት ሃገሬ ጋዜጠኛ ርዩት ዓለሙ ላይ የተፈፀመው ኢሰባዊ ድርጊት ከሁሉም በላይ ከህሊናው ሊጠፋ የማይችል ዘግናኝና አረምኔያዊ ድርጊት መሆኑን ይገልጻል ። ጋዜጠኛው ልጆቹን ከማሳደግ ባሻገር ሃገሩ ላይ ሲኖር ደስተኛ እንዳ ልነበረ በመጥቀስ ክእንግዲ አለ ጋዜጠኛ አለምንህ ዋሴ « ፍትህ እኩልነትና ነጻነት እስኪሰፍን » ሃገር አለኝ ብዬ ፊቴን ወደ ኢትዮጵያ አልዞርም ብሏል ። ጋዜጠኛው ከየትኛውም የፖለቲካ ድርጀት ገለልተኛ ሆኖ ወገኑን ማገልገል እንዳልቻለና የገዢው ስረአት ወሬ አቀባይ ሳይሆኑ ገለልተኛ ሆኖ በነጻነት ኢትዮጵያ ውስጥ ሰርቶ መኖር ለህልውና አደገኛ መሆኑን የራሱን ተሞክሮ በመጥቀስ ያብራራል። በስራው ላይ ይደረግበት በነበረ ጫና የማስታወቂያ ስራዎቹ ለአየር እንዳይበቁ በደል እስከመፈጸምና በሙያው በቀን 10 በር ብቻ ተከፍሎት እንዲሰራ የተገደደበት አጋጣሚ እንደነበረ ለኢሳት በሰጠው መረጃ አጋልጦል። ጋዜጠኛው በአሁኑ ሰዓት አስራኤል ውስጥ ስደት ቤቴ ብሎ መኖር የጀመረ ሲሆን ለኢሳት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ዙሪያ ከኢህአ ዴግ መንግስት ባለስልጣናት በኩል ምንም የተባለ ነገር ባይኖረም ጋዜጠኛው ወደ ሶስተኛ ሃገር ካልተሸጋገረ የደህነት ሁኔታው እንደ ሚያሰጋቸው አይሌ ኢትዮጵያውያን ይገልጻሉ። መንግስት ጋዜጠኞች ላይ የሚወስደውን እርምጃ ተስፋ መቁረጥ የሚሉ እንዚህ ታዛቢዎች ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ ከተዋቂው ጋዜጠና ዳሪዎስ ሞዴና ነጋሽ፡መሃመድ ቀጥሎ የጋዜጠኛ አለምንህ ድምጹ በተፈጥሮ የህዝብን ልብ ሰብሮ የመግባት ሃይል ስላለው ምናልባት መንግስት ደልሎ አሊያም በሃይል ወደ ሃገር ሊመልሰው እንደሚችል ስጋታቸውን ይገልጻሉ ።
- See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/5129#sthash.XCWP4Uc9.dpuf

No comments:

Post a Comment