Translate

Thursday, March 28, 2013

“ሀገሬ ገመናሽ” (ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ፣ ክፍል ሁለት)


በየፍርድ ቤቶችሽ የፍትህ ውርጃ ሲፈፀም ዝም አልሽ።

ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ
ልዕልና ጋዜጣ
ምንጭ፣ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም ብሎግ
በቀደም ሳት ብሎኝ፣
ለመጀመሪያ ልጄ ብቻ የፈረንጅ ሸራ ጫማ ገዝቼ ገባሁ። ያለወትሮዬ ማለቴ ለወትሮው ገበያ የምወጣው ሁለቱንም ልጆቼን ይዤ ስለነበረ ነው። ታዲያ ያን እለታ ማታ ትልቅዋ ልጄ ጫማውን ስትለካ፣ የታናሽ እህትዋ አይን ከሚለካው ጫማ ጋር ሲንከራተት ተመለከትኩ፤ ወይም የተመለከትኩ መሰለኝ። ‹‹ከወደድሽው ላንቺም ይገዛልሻል›› አልኳት፤ የትንሽዋን ልጄን አይን እየሸሸሁ። በውስጤ አድሏዊነት ተላወሰ። በልጅትዋ ህሊና ውስጥ ይህ ስሜት እንደማያድር ባውቅም፣ የእኔን ሃሳብ ግን ቶሎ ላስወግደው አልቻልኩም። አየሽ ሀገሬ? እንኳን ህዝበ አዳምና ሔዋንን በእኩልነት ቤት ሆኜ አኖራለሁ የሚል ሀገር፣ አንድ ተራ ምስኪን ወላጅ እንኳን በጎጆው አድሏዊነት እንዳይሰፍን ይጥራል። አንቺ ግን ሀገሬ! … አንቺ ግን ዝሆንና ጥንቸል እያፋለምሽ ለአሸናፊው ታጨበጭቢያለሽ፤ ትሸልሚያለሽ።

መልካም መሪ ማግኘት ምንኛ መታደል ነው?!


በታምሩ ገዳ

በየትኛውም የእድገት  ደረጃ  ይሁን የፖለቲካ  አመለካከት ወይም የሃይማኖት  ስርአት  ውስጥ ለሚገኝ ማህበረሰብ ሁነኛ መሪ ማግኘት ከእድሎች ሁሉ ትልቁ እድል ነው  ቢባል ማጋነንPope Francis breaks with tradition and refuses to move into a palatial apartment  አያስብልም፡፡
ለዚህ ይመስላል የሮማ  ካቶሊክ ቤ\ክርስቲያን   በቀርቡ 266ኛዋን  መሪ (ፓፓ ) ለመምረጥ የሃይማኖቱ አባቶች  በቫቲካን ከተማ  በተሰባሰቡበት  ወቅት በ 150,000ዎች  የሚቆጠሩ ምእመናን ቀጣዩ የሃይማኖታችን አባት  ማን ይሆኑ? በማለት  የምርጫው ውጤቱን ለማወቅ  በታላቁ  የቅዱስ  ጴጥሮስ  አደባባይ ተሰባስበው የነበረው፡፡ በዚህ የምንፈስ  ቅዱስ መሪነት  በተካሄደው  የመጪው  የቤተክርስቲያኒቱ  መንፈሳዊ አባት መረጣ    ላይ  የብዙዎቹ ምርጫ ሆነው  የቀረቡት  ከ120 ሚሊዮን  በላይ የእምነቱ ተከታዮች  ያሏት አገር  ብራዚል  ከሳኦ ፖሎ ከተማ  የመጡት  አርክቢሾፕ ኦዲሎ ሺረር ነበሩ፡፡

Wednesday, March 27, 2013

“ሀገሬ ገመናሽ” በፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም (ክፍል ሁለት)


በየፍርድ ቤቶችሽ የፍትህ ውርጃ ሲፈፀም ዝም አልሽ።

በፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም (ክፍል ሁለት)
በቀደም ሳት ብሎኝ፣
ለመጀመሪያ ልጄ ብቻ የፈረንጅ ሸራ ጫማ ገዝቼ ገባሁ። ያለወትሮዬ ማለቴ ለወትሮው ገበያ የምወጣው ሁለቱንም ልጆቼን ይዤ ስለነበረ ነው። ታዲያ ያን እለታ ማታ ትልቅዋ ልጄProfessor Mesfin Woldemariam is one of Ethiopia's well-known intellectuals ጫማውን ስትለካ፣ የታናሽ እህትዋ አይን ከሚለካው ጫማ ጋር ሲንከራተት ተመለከትኩ፤ ወይም የተመለከትኩ መሰለኝ። ‹‹ከወደድሽው ላንቺም ይገዛልሻል››አልኳት፤ የትንሽዋን ልጄን አይን እየሸሸሁ። በውስጤ አድሏዊነት ተላወሰ። በልጅትዋ ህሊና ውስጥ ይህ ስሜት እንደማያድር ባውቅም፣ የእኔን ሃሳብ ግን ቶሎ ላስወግደው አልቻልኩም። አየሽ ሀገሬ? እንኳን ህዝበ አዳምና ሔዋንን በእኩልነት ቤት ሆኜ አኖራለሁ የሚል ሀገር፣ አንድ ተራ ምስኪን ወላጅ እንኳን በጎጆው አድሏዊነት እንዳይሰፍን ይጥራል። አንቺ ግን ሀገሬ! … አንቺ ግን ዝሆንና ጥንቸል እያፋለምሽ ለአሸናፊው ታጨበጭቢያለሽ፤ ትሸልሚያለሽ።

ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ፤ አጭር የሕይወቱና የጽሑፉ ታሪክ


(በሰሎሞን ተሰማ ጂ.)

Email: solomontessemag@gmail.com
ማንም በዕድሜው ብዛት አያስጠራም ስሙን
በጥቂቱም ዕድሜው ይሠራል ሐውልቱን፡፡
ታሪክ ሲያበላሸው ረጅሙም ያጥራል፣
ታሪክ ሲያሳምረው አጭሩም ይረዘማል፤
ብዙ ዘመን ቢኖር ዕድሜውም ቢበዛ፤
በሳቅ በጨዋታ ዋዛን በፈዛዛ፣
ሲለዋውጥ ኖሮ ሃሳቡን ሳይገዛ፣
እንዲሁ ይቀራል እንዲያው እንደዋዛ፡፡
(“ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ፤ አጭር የሕይወቱና የጽሑፉ ታሪክ” (2004)፤ ገጽ 191)
ከላይ የተጠቀሱት ስንኞች የማንን “ዕድሜ” እና “ታሪክ” ለማሳመር እንደሚበጁ ለመወሰን አያዳግትም፡፡ ሥንኞቹ ጉልሕ አጽንዖት የሚሰጡት ዕድሜው ስላልበዛው ሰው ነውና፤ የዚህ መጽሐፍ ደራሲም ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ “38 ዓመት ከ10 ወር ሊሞላው 4 ቀን ጎደል ነበር”፡፡ ለአንድ “ሩቅ አስቦ፣ ቅርብ ላደረ” ሰው የሚስማማ ዐርኬ ነው፡፡ ሌሎቹ በዚህ የመጽሐፍ ግምገማ ውስጥ የምናወሳቸው ሁለት ሰዎች፣ ከዚህ “አታላይ ዓለም” ሲለዩ ሃምሳ ሲደመር ሦስትና ለሰባ አንድ ፈሪ ነበሩ፡፡

Ethiopia: Prime Minister Bereket Simon


Ethiopia: Prime Minister Bereket Simon

by Amanuel Biedemariam
After the late genocidal dictator Meles Zenawi was rumored to have been sick, incapacitated or dead, Bereket SimonBereket Simon direct Ethiopian political direction to suit his needs. used the time cunningly to direct the course of the current Ethiopian political direction to suit his needs and the needs of few of his close allies. I have in the past written that “the End of TPLF is here”; and current political developments in Ethiopia prove that in deed, has happened. TPLF revolution, Gedli Tigray is over, caput because Bereket Simon is the undisputed victor for now.

በምንሊክ ሆስፒታል የኩላሊት ስርቆት ይካሄዳል ተባለ !


ኩላሊት ለመስረቅ ሙሉ መሳሪያና የኩላሊት ባለሙያ ያስፈልጋል – የሆስፒታሉ ባለሙያ በምንሊክ ሆስፒታል ኩላሊት ተሰርቋል በሚል በቀረበ አቤቱታ የተነሳ በሆስፒታሉ የአስክሬን ምርመራ ክፍል ላይ ምርመራ እንደተካሄደ ምንጮች የገለፁ ሲሆን፣ የሆስፒታሉ ባለሙያዎች የኩላሊት ስርቆት ሊካሄድ አይችልም ሲሉ አስተባበሉ፡፡ የመኪና አደጋ ደርሶበት በምንሊክ ሆስፒታል ሲታከም የነበረ ሰው ህይወቱ በማለፉ የሟች ቤተሰቦች ለፖሊስ የሚቀርብ ማስረጃ ከሆስፒታሉ ጠይቀው ነበር በማለት የገለፁ ምንጮች እንደሚሉት፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ የተካሄደው የአስከሬን ምርመራ በቤተሰቦች ላይ ቅሬታና ጥርጣሬ እንደፈጠረ ይጠቁማሉ።
ጉዳዩም ወደ ፖሊስና ወደ ፀረ ሙስና ኮሚሽን እንዳመራ ምንጮቹ ጠቁመው፣ መርማሪዎች በሆስፒታሉ ተገኝተው ቅኝት እንዳካሄዱና ባለሙያዎችን እንዳነጋገሩ ገልፀዋል። ከፖሊስና ከፀረ ሙስና ኮሚሽን መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ፣ በሃላፊዎች አለመገኘት ምክንያት ባይሳካም፤ የሆስፒታሉ ባለሙያዎች በበኩላቸው መርማሪዎች ወደ ሆስፒታሉ መጥተው እንዳነጋገሯቸው ጠቅሰዋል። አስከሬን ላይ ተገቢውን ምርመራ እንደሚያከናውኑ የሚገልፁት የሆስፒታሉ ባለሙያዎች፤ “በህክምና ወቅት ያልተከፈተውን የሟች አካል፣ በአስከሬን ምርመራ ወቅት እንዴት ይከፈታል?” የሚል ቅሬታ ከሟች ቤተሰቦች በተደጋጋሚ ይቀርባል ሲሉ ተናግረዋል።

Tuesday, March 26, 2013

በአረመኔው የወያኔ አገዛዝ በግፍ እስር ቤት የታጎሩት ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከፍተኛ ችግር ላይ መውደቃቸው ታወቀ


በአረመኔው የወያኔ አገዛዝ በግፍ እስር ቤት የታጎሩት ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከፍተኛ ችግር ላይ መውደቃቸው ታወቀ

ድምጻችን ይሰማ የሚል መፈክር አንግበው ላለፉት አስራ ሶስት ወራት አፋኙን የወያኔ አገዛዝ መቆሚያና መቀመጫ በማሳጣታቸው በጭካኔ እስር ቤት የተጣሉት ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ችግር ላይ መውደቃቸውን ዘጋቢያችን ከአዲስ አበባ ባስተላለፈልን ሪፖርት ገለጸ፣ ፣ እንደዘጋቢያችን ሪፖርት በዘረኛውና አረመኔው የወያኔ አገዛዝ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ታፍሰውና ማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ በግፍ ታስረው የሚገኙት ሙስሊም የዩኒቨርሰቲ ተማሪዎች ፣ ቤተሰቦቻቸው ያሉበትን ቦታ ባለማወቃቸው በቀለብ እና በልብስ እጦት እየተቸገሩ ነው ብሏል።
ዘጋቢያችን እንደገለጠው በአቃቂ እስር ቤት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊም ተማሪዎችና መምህራን እስር ቤቱን አጨናንቀው እንደሚገኙ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ፣ ከነኝህ ታሳሪዎች ውስጥ እጂግ በርካቶቹ ቶርቸር ( አሰቃቂ ድብደባ) ተፈጽሞባቸዋል። ይህም አልበቃ ብሎ ተማሪዎቹ በአሁኑ ጊዜ የረባ ምግብ አጥተው በመሰቃየት ላይ እንደሚገኙና ልብሶቻቸው በላያቸው ላይ እያለቁባቸው ለእርዛት እየተዳረጉ እንደሆነም ታውቋል።