Translate

Monday, November 10, 2014

እኛ እነሱና እነዛ

እኛ እነሱና እነዛ ( ሄኖክ የሺጥላ )
በአማርኛ ልጽፍ በ አዴ ይርገጡ ቡና ቀኑን እንዴት አደርክ ብዬ መተየብያዬን ስቤ ጉልበቴ ላይ ጣል አደረኩት ። እንደ ስሙ ( ላፕ ቶፕ ) የሚባለው አይነት የ አቀማመጥ ስርዓት ላይ ነው ያለው ፣ መሃል ላይ የእንግሊዘኛ ከራማ ካልገባሁ ፣ ሄኖክ ሙት በእንግሊዘኛ ፣ ዛሬ በእንግሊዘኛ ሲለኝ ፣ ቆይ ቆይ ትንሽ ባገርኛ ከዛ በእንግሊዘኛ ብዬ ፣ ራሴን እንደምንም ተቆጣጥሬ በአማርኛ መጻፍ ቀጠልኩ ።
እና ስለ ትግል ፣ ስለ ትግሬ ወያኔዎች እና ስለመሳሰሉት መጻፍ ጀመርኩ ። በነገራችን ላይ የራሳቸው የነበረከት ስምዖን አመለካከት ምን ይላል መሰላችሁ " አንድን ነገር ደጋግሞ በመናገር ለውጥ ማምጣት ይቻላል "። የምትናገረው ነገር ደሞ ያልተነገረ ወይም የተዳፈነ እውነት የሆነ እንደሆነ በቃ ምን ሊሆን እንደሚችል አስብ ። ትግሬዎች አላልኩም ፣ እደግመዋለሁ ትግሬዎች አላልኩም ፣ የትግሬ ወያኔዎች! ። ወያኔ ለሚለው ምን አይነት ወይም የነማን ወይም ከማን ለሚለው ትንሽ ገላጭ ነው ጣል ያደረኩበት ። አሁን ይሄ ገላጭ እንዲህ የሚያንጫጫ ነበር ። እውነት ባይሆን ኖር አንተ የትግሬ ወያኔ የሆንከው ወንድሜ ምክንያትህን በጠራና እና አመክኖዊ በሆነ መንገድ ባቀረብክ ። ግን ምንም ልታቀርብ የምትችለው ነገር የለህም ። እስኪ ንገረኝ ላለፉት 23 አመታት ትግራይ ውስጥ የተካሄድ ሰልፍ ካለ ፣ እስኪ ንገረኝ መለስን በመቃወም ሰልፍ የወጡ የትግራይ ልጆች በየትኛው እስር ቤት እየተሰቃዩ እንደሆነ ፣ እስኪ ንገረኝ በነጻ ፕሬሱ ዘመን ( ነብሱን ይማረውና ) ፣ ትግራይ ውስጥ በትግርኛ ይታተም የነበረ የተቃውሞ ጋዜጣ አንብበህ ከነበረ ፣ እስኪ ንገረኝ መለስ " እንኩዋንም ከናንተ ተፈጠርኩ ሲል " ይሄን ነገር እንቃወማለን ብለህ ሰልፍ ወጥተህ ከሆነ ፣ እስኪ ንገረኝ በትግራይ የሰማእታት ሃውልት ሲሰራ ፣ የትግራይ ሕዝብ ብቻውን ደርግን ጥሎ አዲስ አበባ የገባ እስኪመስል ድረስ ሌላ ቦታ አንድም መታወሻ እና ማስታወሻ ያላደረከው ልክ አይደለም ብለህ ከሆነ ፣ ባንጻሩ ለትግራይ የድል ሰማዕታት ፣ ለኦሮሚያ አኖሌ ፣ እስኪ ንገረኝ ወያኔ ደም የሚ ያቃባ ን ድርጊቶችን ሲፈጽም ፣ አንተን አልመርጥህም ፣ ከኔ ዘር ብትሆንም ከኔ ወገን ግን አይደለህም በለኸዋል ወይ ? እስኪ ንገረኝ የብሔር ብሄረስቦች እኩልነት አረጋገጥኩ የሚል ስርዓት ከጽዳት እሰከ ጠቅላይ ሚንስቴር ባንድ ጎሳ ተሞልቶ ሀገሪቱን የወፌ ላላ ሲገርፉዋት ወጥተህ ይሄ ነገር ልክ አይደልም ብለህ ተናገርክ ወይ ፣ እስኪ ንገረኝ ስልጣን ፣ ሥራ ፣ ኑሮ ፣ መሬት ፣ ልመና እንኩዋ ሳይቀር ከኛ ሌላ ላሳር ሲሉ፣ " አይ አንተ የኔ መንግስት አይደለህም!" ፣ አንተ ትወክለኝም ብለህ የማታውቅ የትግራይ ወያኔ ሆይ ፣ ትግሬና ወያኔ እንዳልለይ ያረከኝ አንተ ራስህ ነህ ፣ ምክንያቱም መስመሩን አጠቆርከው ፣ በኔና በህውሃት መሃከል ምንም አይነት ልዩነት የለም አልከን ፣ ባፍህ ሳይሆን በምግባርህ ፣ በዝምታህ ፍቅርህን ገለጽክ ፣ ያንተ ቁስል የሚያመረቅዘው ወያኔን ሲነኩብህ ሆነ ፣ መግዛት የነጻነት ውጤት መሆኑን ረሳህ ፣ እኛ ያንተ የስልጣን ጭሰኞች እንድንሆን ፈለክ ፣ ስላልፈራሁ ተበሳጨህ ።
እመነኝ አዲስ አበባም እያለሁ ፈርቼህ አላውቅም ፣ ፑሽኪን፣ ስድስት ኪሎ የባህል መአከል ፣ አሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲዝ ፣ የጎንደር በርሃ ፣ የአርማጮ ንዳድ ይመስክሩብኝ አልፈራህም ። መሬት እንዳይወሰድ ፣ ወይም መኪናዬ እንዳይቀማ ወይም ሱቄ እንዳይዘጋ ብዬ ዝም እንድል አታደርገኝም ። እነዚህን ሁሉ ማድረግ እችል ነበር ግን አላደርገውም ፣ አንተን እንዲመች መንገድ አልቀፍትልህም ። አባይ አባይ ስትል ሳቄ ይመጣብኛል ፣ ንስሐ ይሆን ድልድይ ያፈርስ የነበረ ተገንጣይ እና ነጣጣይ ዛሬ የበግለምድ ለብሶ አባይ አባይ የሚለኝ ፣ ስለ መንገድ እና አበባ ስታወራ አንተ ሳትሆን የሚሰሙህ ሆድ አደሮች ይቀፉኛል ። ከ ወለጋ የመጣ አንድ ኦሮሞ መንዝ ሄዶ እንዳይሰራ እያደረክ ፣ ከ መንዝ የሄደ አንድ አማራ ጋንቤላ እንዳይቀመጥ እየወሰንክ መንገድ መንገድ ስትል አዎ ይገርመኛል ። ሰዎቹን ስታፈናቅሉ በቶሎ ለማመላሰስ ነው እንዴ መንገድ የሰራከው ።
ሃሳብ ሁለት ለወዳጆቼ
ወዳጆች ሆይ ከአሁን በሁዋላ አትምከሩኝ ፣ የመፍራት መብታችሁ በሕግ የተጠበቀ ነው ፣ እኔን ለመምከር የሚያስችል ስብእና ግን ያላችሁ አይመስለኝም ። ልክ አይደለህም ሳይሆን በዚህ በዚህ ምክንያት ይያልከው ልክ አይደልም በሉኝ ። እኔ ትግሬ ሁሉ ወያኔ ነው አላልኩም ፣ ከሞሆን የሚያግደው ምንም ነገር እንደሌለም አውቃለሁ ፣ የቫይረሱ ተሽካሚ ለሆኑት ነው የምጽፈው ። ለነሱ ፣ ሞቴ ድሎት ለሆነባቸው ፣ ደሜ ላደመቃቸው ፣ ለነሱ ነው ! አዎ በስቃዬ ሳቅ ግን አብረከኝ አትስቅም ፣ ከአሁን በሁዋላ በእድርም በሰርግም አታውቀኝም ነው መልክቴ። አብሮ ለመኖር መጀመሪያ መኖር ያስፈልጋል፣ ለማፍቀር የሚፈቀር ነገር መኖሩ የግድ ነው ፣ እኔ ቁስ አላፈቅርም ፣ ሰው ሆኖ እንደ እንሰሳ የሚያስብን በፍቅር ለማሸነፍ " በፍቅር ያመነ መስቀሉን ይዞ ጉና ተራራ ላይ ከኔ ጋ ይውጣ " ፣ የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ ወያኔን መፍራት ነው ብዬ እንድሰብክ ከሆነ ፣ ወንድሜ ሙት ተሳስተካል ! በጣም ተሳስተካል ! ለዚህ ስህተትህ ኩርኩም ሳይሆን መፈንቅለ መንግስት ነው የሚገባህ ፣ ያም ይሆን ዘንድ እስከ ምሞት ዝም አልልም ፣ ብሞት እንኩዋ ስራዬ እንዲናገር አርጌ ነው የምሞተው ( ባለ ራአይ ማለት ታዲያ ይሄ አይደል ?!) ። አንተ ስለ ፍቅር ስታወራ እነሱ ባንተ ፍቅር መቃብርህን እየቆፈሩ ነው ፣ እነዚ ሰዎች ( ወያኔዎች ) ዶ/ር ጥላሁን እንዳለሁ ነቀርሶች ናቸው! አንተ ስለ አንድነት ስታወራ እነሱ በቤተሰብ ደረጃ እንዴት አንተን ማጥፋት እንዳለባቸው እየዶለቱ ነው ። ከአሁን በሁዋላ ወንጀል መስራት ለነሱ የህልውና ጉዳይ ነው ፣ ታላቂቱ ትግራይ በህዝቦች እኩልነት እንጂ በጎሳ የበላይነት አትመሰረትም ፣ በደም የገነባኸው ፣ በደም ይፈርሳል ፣ ሰርቀህ ያካበትከው ይሰረቃል ፣ አንዳችም ያንተ ያልሆነ ነገር ያንተ አይሆንም ፣ ደብረዘይትን የሚያክል መዝገብ አዘጋጅተን ፣ ጆሮ ውስጥ ያለው ኩክ እንክዋ ያንተ ካልሆነ ትመልሳለህ ። የትግራይ ታይዋን በኢትዮጵያውያኖች ጥረት እንጂ በኢትዮጵያውያኖች መከራ አትገነባም !!! የበሰበሰ ዝናብም ጥቁር ሰማይም አይፈራም አንተ ግን ከቻልክ መብረቅ ሁን ነው ! ከሰማህ ስማ ካልሰማህ የዛሬ 10 ዓመት አንተው ራስህ እኔን ሆነህ ታገኘዋለህ ። በደል የሰውን ስሜት ይቀይራል ። ጭካኔ ጨካኝ ያደርጋል ። ሩዋንዳ የተረት ምድር አይደለችም ፣ ላይቤርያ ዝም ብላ የደረሰችበት መከራ ውስጥ አልገባችም ። የማያልቅ መከራ ልብን ያደነድናል ፣ ጨቁዋኝ ጊዜው ሲደርስ ረሳው በየ ጎዳና ላይ ይሳባል ፣ ይሄን ከመሆኑ በፊት ወያኔን ወለ በለው ፣ ሂድ ከዚ በለው ፣ አሳየኝ ፣ ምርጫው ያንተ ነው ። የምለው ምን ያህል እውነት እንደሆነ አንተ ይሄን በ ኮምፒ ተርህ ላይ የምታነበው ታውቀዋለህ !

1 comment:

  1. I nearly missed out on this one. Thank you Tesfaye Zenebe. Well done Henok Yeshitila. Tell them point blank as it is!!!!

    ReplyDelete