Translate

Sunday, January 31, 2016

በዲሲ የአርበኞች ግንቦት 7 የቀጥታ ስብሰባ ይሄን ከፍተው ይከታተሉ jan 31 2016- watch live


ሰበር መረጃ – የአባይ ግድብ እና የቦንድ ገንዘብ ዘረፋ (ወያኔ)

dam-467
(Satenaw) — የአል ጀዚራ ባልደረባ የሆነዉ ሃሰን ሁሴን  (Hassen Hussein) እንደዘገበዉ ጃንዋሪ 8 ላይ ግብጽ የአባይ ግድብ ግንባታ እንዲቋረት ጠይቃለች ይህዉም በሁለቱ ሐገራት መካከል ዉስጥ ለዉስጥ እየተካረረ የመጣ ዲፕሎማሲያዊ ጸብ ወደ ተለያየ አቅጣጫ እንደሚሄድ ሲነገር ቆይቶ ሰንብቶ ነበር።

የኃይለማርያም ደሳለኝ ስድስተኛው አማካሪ ከትግራይ – ብርሃነ ገ/ ክርስቶስ (የአርከበ እቁባይ አማች)

arekebe
ከኤርሚያስ ለገሰ
እነሆ! ዛሬ ደግሞ ” በሚኒስትር ማእረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዩ መልእክተኛ ” የሚል ሹመት ሰማን። የአዲሱ ቦታ ስልጣን እና ሃላፊነቱ ባይገለጵም ሹመቱ ከተሰጠው ሰው ማንነት ተነስቶ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አያዳግትም። ቢያንስ ቢያንስ ” የዶሮ ወጥ መልእክተኛ” እንደማይሆን ይጠበቃል።

Thursday, January 28, 2016

ኢትዮጵያ “ነፃነት የሌለባት”፤ ኤርትራ “ከክፉዎች የከፋች” ተባሉ

በዓለም ዙሪያ የሚሰማው የምጣኔ ኃብት ድቀት እና የማኅበራዊ ነውጥ ፍራቻ አምባገነን መንግሥታት በአውሮፓ አቆጣጠር ባለፈው 2015 ዓ.ም ይበልጥ አፋኝና ጨቋኝ እንዲሆኑ ሰበብ ሳይሰጣቸው እንዳልቀረ ዛሬ የወጣ የዓለም የነፃነት ሁኔታ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ፍሪደም ሃውስ የሚባለው ነፃ ቡድን በዚህ ሪፖርቱ የሃገሮችን የዴሞክራሲያዊ የነፃነት ይዞታዎች ገምግሞ በደረጃ አስቀምጧቸዋል፡፡ አምባገነን አገዛዞች ባለፈው የአውሮፓ ዓመት በ2015 ዓ.ም ይበልጥ የከፉ መሆናቸውን ይህ ዛሬ የወጣ የዓለም የነፃነት ይዞታ ሪፖርት ይናገራል፡፡

ር'ዮት አለሙ እንደ ክርስቶስ ደሞ እንደ በላይ ( ሄኖክ የሺጥላ )

ር'ዮት አለሙ እንደ ክርስቶስ ደሞ እንደ በላይ ( ሄኖክ የሺጥላ )

ጋዜጠኛ 'ና መምህርት ር'ዮት ዓለሙ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋ ታሪኳን ( ያሳለፈችውን መከራ ፣ እንግልት ፣ ስቃይ እና አስር ) በቅንጭብ ካካፈለችበ የኢሳት ማህደር ውስጥ ገብቼ ቃለ ምልልሷን አደመጥኩ ። እኔ በግሌ ቃለ ምልልሱ ፥ ስለ ወያኔ ( ወይም የ ዘንድሮ ትግሬ ምንነት) ስላለኝ እምነት ( ኣቋም ) ማረጋገጫ ከመሆን ውጪ ሌላ ነገር አላገኘሁበትም ። እንደ ሰው ፣ እንዲሁ አንዳንዴ "እስኪ እኔ ትግሬ ብሆን ኖሮ ሄኖክ የሺጥላ የሚጽፈውን "ትግሬ ተኮር" ጽሑፎች እንዴት ነበር የማያቸው?" ብዬ ራሴን ደግሜ ደጋግሜ ጠይቄ ላገኘሁት መልስ የ ር'ዮት ቃለ ምልልስ ስጋ ለበስ ባለ እስትንፋስ ማስረጃ በመሆን ለወያኔ -ትግሬ ሊኖረኝ የሚችለውን ቅንጣት "ምናልባችን" ጠራርጎ የወሰደ ፣ የማንነታቸው ፍጹም ማረጋገጫ ሆኖም አግኝቼዋለሁ ።

Tuesday, January 26, 2016

ኢንሳ የአየር ላይ ፎቶ በማንሳት ላይ የሚገኘው ለሱዳን ተሰጥቷል የሚባለውን አልፋሽጋ ተብሎ የሚጠራውን አካባቢ መሆኑ ታወቀ

ጥር ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ካለፈው ጥር ወር መግቢያ ጀምሮ የአየር ላይ ፎቶ እየተነሳ ያለው አካባቢ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ” ኢትዮጵያ መሬቱ የእኛ መሆኑን እውቅና ሰጥታለች” በማለት ለአልጀዚራ የተናገሩት አልፋሽጋ እየተባለ የሚጠራው ቦታ መሆኑ ታውቋል።

Ethiopian Border Affairs Committee
ትናንት ኢሳት የመረጃና ደህንነት ኢንፎረሜሽን ባለሙያ በማናገር በሰራው ዘገባ ላይ በአሁኑ ሰአት የአየር ላይ ፎቶ ለማንሳት ምልክቶችን መሬት ላይ የማስቀመጡ ስራ የሚከናወነው 365 ኪሜ ርዝመት ባለው ቦታ ላይ መሆኑን ቢዘግብም፣ ይህ ርቀት ግን የአየር ላይ ርቀትን የሚያመለክት እንጅ የመሬትን እርቀት የሚያመለክት ባለመሆኑ ማስተከከያ እንዲደረግበት ጠይቀዋል። በመጀመሪያው ሂደት ድንበር የማካለሉ ሂዳት የሚከናወነው 725 ኪሜ ርዝመት ላይ ባለው መሬት ላይ ሲሆን፣ ይህም አካባቢ ሱዳን የኢትዮጵያ መንግስት የእኔ መሬት መሆኑን አምኖልኛል በማለት የገለጸችው አልፋሽጋ እየተባለ የሚጠራውን ለም መሬት የሚያካትት ነው።

የኢትዮጵያ ሙስሊም ፈተና በ224 ደቂቃዎች

(ዘላለም ክብረት)

የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እና ተባብራችኋል ተብለው የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን 
© ማሕበራዊ ሚዲያ

ክፍሉ ከኮሪደሩ ላይ ከተንጠለጠለ አምፖል በሚመጣ ብርሃን ፈገግ ብሏል፡፡ እኔም ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ወደ ክፍሉ ስገባ ከክፍሉ አንደኛው ጫፍ ላይ አንድ ቀጠን ያለ ሰው ድምፁን በትንሹ ከፍ አድርጎ ቁርዓን ‹እየቀራ› ነበር፡፡ በክፍሉ ሌላኛው ጫፍ ላይ ደግሞ አንድ ፍራሽ፣ አንድ የውሃ ጀሪካን እና ትንሽ ልብሶች በፌስታል ውስጥ ተቀምጠዋል፡፡ በሌላኛው የክፍሉ ጫፍ ደግሞ የሽንት ባልዲ – ሽታውን ለመቀነስ ሲባል በግማሽ ውሃ ተሞልቶ ተቀምጧል፡፡ ክፍሉ ውስጥ እንደገባሁ አንዱ ጫፍ ላይ ትንሽ ቆም ካልኩ በኋላ በክፍሉ ውስጥ ያገኝሁት ብቸኛው ሰው ፍራሹ ላይ እንድቀመጥ በእጁ ሲጠቁመኝ ቁጭ አልኩ፡፡ ፍራሽ ላይ እንደተቀመጥኩ በፍራሹ ጫፍ ላይ የጆን ግሪሻም ‘The Last Juror’ መፅሃፍ ተቀምጦ አየሁት፤ አንስቼ ስመለከተው ክፍሉ ውስጥ ያገኘሁት ሰው ቁርዓን መቅራቱን ጨርሶ እንግሊዝኛ እችል እንደሆነ ጠይቆኝ ማውራት ጀመረ፡፡