
ድርጅትን በተለያዩ አገሮች ማስመዝገብ (ኦፍሾር ምዝገባ) በራሱ ወንጀል ባይሆንም ጥቂት የማይባሉ ኩባንያዎችና ባለቤቶቻቸው ግን ይህን የሚያደርጉት ግብር ለማጭበርበር፥ በሙስናና በሌሎችም ወንጀሎች የተገኘ ሀብትን ለመሰወር ወይ በድብቅ ወደ ሕጋዊነት ለማሸጋገር ሊሆን እንደሚችል ብዙዎች ይናገራሉ። “የፓናማ ዶሴዎች”ን ይፋ መሆን ተከትሎ አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አገሮች ሕጎቻቸውን ወደማጥበቅና በዶሴዎቹ የተጠቀሱትን ግለሰቦች ወደመመርመር ሲሄዱ፥ ስማቸው በዶሴዎቹ በመገኘቱ ስልጣን እስከመልቀቅ በሚያደርስ ውዝግብ ውስጥ የተዘፈቁ ግለሰቦች፥ ለውስጣዊ ውዝግብ የተጋለጡ ድርጅቶች ብዙ ናቸው።