Translate

Wednesday, May 11, 2016

ኢትዮጵያ በፓናማ ዶሴዎች!

panama papersዋዜማ ራዲዮ- “የፓናማ ዶሴዎች”  (The Panama papers) በመባል የሚታወቁትን ምስጢራዊ ሰነዶች ለህዝብ ይፋ ያደረገው አለማቀፉ የምርመራ ጋዜጠኞች  ቡድን (International Consurtium of Investgative Journalists ) በዚህ ሳምንት ያሰባሰባቸውን ተጨማሪ መረጃዎች ይፋ አድርጓል። መረጃው ሞሳክ ፎንሲካ (Mossack Fonseca) በተባለ ተቋም አማካይነት ድርጅቶቻቸው ከአገራቸው ውጭ በተለይም በፓናማና በሌሎችም ልል የታክስ ሕግ ባለባቸው አገሮችን ያስመዘገቡ ግለሰቦችን ማንነት ይፋ ለማድረግ የሞከረ ነው።
ድርጅትን በተለያዩ አገሮች ማስመዝገብ (ኦፍሾር ምዝገባ) በራሱ ወንጀል ባይሆንም ጥቂት የማይባሉ ኩባንያዎችና ባለቤቶቻቸው ግን ይህን የሚያደርጉት ግብር ለማጭበርበር፥ በሙስናና በሌሎችም ወንጀሎች የተገኘ ሀብትን ለመሰወር ወይ በድብቅ ወደ ሕጋዊነት ለማሸጋገር ሊሆን እንደሚችል ብዙዎች ይናገራሉ። “የፓናማ ዶሴዎች”ን ይፋ መሆን ተከትሎ አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አገሮች ሕጎቻቸውን ወደማጥበቅና በዶሴዎቹ የተጠቀሱትን ግለሰቦች ወደመመርመር ሲሄዱ፥ ስማቸው በዶሴዎቹ በመገኘቱ ስልጣን እስከመልቀቅ በሚያደርስ ውዝግብ ውስጥ የተዘፈቁ ግለሰቦች፥ ለውስጣዊ ውዝግብ የተጋለጡ ድርጅቶች ብዙ ናቸው።

ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተወራረደና የተበላሸ ሂሳብ ያለው ንግድ ባንክ ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ወጪ ማውጣቱ ታወቀ

Image result for commercial bank of ethiopia
ለኢሳት የደረሰው የባንኩ የውስጥ ኦዲት ሪፖርት እንደሚያሳየው በበጀት አመት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2013 እና 2014 ባንኩ ያላወራረደው 11 በሊዮን ብር እንዲሁም የተበላሸ ገንዘቡ 1 ቢሊዮን ብር ቢደርስም፣ የባንኩ ባለስልጣናት ከተመደበላቸው መደበኛ በጀት ውጭ 729 ሚሊዮን ብር አውጥተዋል። “ሙስናን በመዋጋት አገራችንን ከዘላለማዊ ከእዳ እንታደግ “ በሚል የባንኩ ሰራተኞች የውስጥ እንቅስቃሴ የጀመሩ ሲሆን፣ ከመንግስት ባለስልጣናትና ከህወሃት ታዋቂ ባለሀብቶች ጋር ከፍተኛ የጥቅም ቁርኝት የፈጠሩት የንግድ ባንኩ ስራ አስኪያጅ፣ ባንኩንና አገሪቱን ለከፍተኛ እዳ እየዳረጉዋት ነው ይላሉ።

በአርባምንጭ የነጭ ሳር ፓርክ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ከ20 ያላነሱ የመንግስት ታጣቂዎች ተገደሉ


የአካባቢው ታማኝ ምንጮች እንደገለጹት ታጣቂዎቹ ባደረሱት ድንገተኛ ጥቃት 20 የመንግስት ወታደሮች ሲገደሉ፣ በርካቶች ደግሞ ቆስለዋል። ከተገደሉት መካከል የአካባቢው ወታደራዊ አዛዥም ይገኝበታል። የተኩስ ልውውጡ ለረጅም ሰአታት የቀዬ መሆኑን የሚናገሩት ምንጮች፣ በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዱ የመንግስት ታጣቂዎች ወደ ህክምና ተወስደዋል።
የመንግስት የጸረ ሽብር ግብረሃይል ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ ከኤርትራ የተንቀሳቀሱ ሃይሎች በሞያሌ በኩል ወደ አርባምንጭ ጫካ በመግባት ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ገልጿል። መንግስት በቁጥጥር ስር የዋሉና የተገደሉ ታጣቂዎች መኖራቸውን ቢገልጽም ፣ በአሃዝ ከመግለጽ ተቆጥቧል። ይሁን እንጅ የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ድንገተኛ ጥቃቱን የፈጸሙት የታጠቁ ሃይሎች፣ ጥቃቱን ካደረሱ በሁዋላ ከአካባቢው ተሰውራል። ይህን ተከትሎም ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ የከተማው ሰዎች እየታፈሱ ተወስደዋል።
አርበኞች ግንቦት 7 ጥቃቱን እንደፈጸመ በከተማው እየተወራ ቢሆንም፣ ንቅናቄው እስካሁን የሰጠው ይፋዊ መግለጫ የለም።

ሰበር ዜና..አል ሸባብ የኢትዮጵያን ወታደሮች ጠለፈ


ወደ ባይ_ዶዋ አካባቢ የተወረወሩ የአል_ሸባብ ታጣቂዎች ሶስት የኢትዮጵያን ወታደሮች አግተዉ የአል_ሸባብ ወታደራዊ ጣቢያ ( base ) ወደ ሆነው ኢል_ ቡር ( El_bur ) መዉሰዳቸዉን የሚጥቁሙ መረጃዎች ለወያኔዉ የምስራቅ እዝ ወታደራዊ ደህንነት ደርሰዉታል!
በቅኝት ላይ ተሰማርተዉ ከነበሩ ጥቂት የዝዝዉር ወታደሮች መካከል ሶስቱ መሰወራቸዉን ተንተርሶ ፍለጋ ቢደረግም ምንም አይነት ፍንጭ ጠፍቶ የነበረ ሲሆን ወታደሮቹ በአል_ሸባብ መጠለፋቸዉን የሚጠቁሙ መረጃዎች ከወደ ኢል_ቡር መንደር እንደደረሰዉ የስምሪት አዛዡን ተንተርሶ አንድ የምክትል መቶ አለቅና ሌሎች ተራ ወታደሮች መጠለፋቸዉን በሶማሌያ የኢትዮጵያዉ ጦር አዛዥ ኮነሬል የማነገብረ ማርያም ለምስራቅ እዙ አሳዉቋል።
በታህሳስ ወር 2006 እ.ኤ.አ የተመሰረተዉ አል_ሸባብን ማጥፋት ማለት መላዉ የሶማሌያን ሕዝብ ማጥፋት ማለት ነዉ! ያሉት ምንጫችን አክለዉ አል_ሸባብ ማለት እጅግ ጨካኝና አረመኔ የጥፋት ቡድን ነዉ። ከአልሸባብ ጋር የሚደረጉ ትንቅንቆች በሙሉ ከሶማሌያ ህዝብ ጋር የሚደረግ ትንቅንቆች ናቸዉ። ምንም እንኳን በዚህ በሶማሌያ ያሉት የኢትዮጵያ ወታደሮች መጠን ቢቀነስም የአል_ሸባብ ድንገተኛ ጥቃት ግን ፈጽሞ አልቀነሰም አሁን የተጠለፉት ወታደሮቻን የሚጠብቃቸዉ የከፋ ሞት ብቻ ነዉ ብለዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

Tuesday, May 10, 2016

ይህ ምሁር የት ነው ያለው??

በስዩም ወርቅነህ
የቀድሞ ሟች ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከምርጫ 97 ሦስት ዓመት በፊት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሁራን በሰበሰበበት ወቅት ታሪካዊ ንግግር ያደረገው በፎቶ የምትመለከቱት ምሁር ቪድዮ ብዙ ሰው በማህበራዊ ድረ-ገፆች ሲወያይበት፣ ሲያካፍል፣ ሲያዳምጠው ቆይቷል ሆኖም ይህ ምሁር የት እንዳለ ሲጠይቅ አላየሁም። እሱም እንደተነበየው ኢትዮጵያ አዘቅት ውስጥ ስትወድቅ ምንም አይነት አስተያየት ሲሰጥ አልተመለከትኩም። እውን ይህ ምሁር በህይወት አለን? ወይስ መሰሪው አፓርታይዱ ፋሽስት የወያኔ/ኢህአዴግ ስርዓት እንደ ሌሎች ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን አስሮታል? ገሎታል?Confronting Meles Zenawi
ለሁሉም መራጃ ያላችሁ ብታሳውቁን። አልያም ሚዲያዎች ይህን ምሁር ምን ላይ እንዳለ ሙያዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ በኢትዮጵያ ህዝብ ስም እጠይቃችኋለሁ። ይህ ምሁር ሃገራዊ ግዴታውን ለመወጣት በድፍረት በመናገሩ የደረሰበት ነገር ካለ የኢትዮጵያ ህዝብ ማወቅ መቻል አለበት።
በህይወት ካለና በሚዲያ መቅረብ የማይችል ከሆነ ፎቶውን በማስደገፍ መረጃ ስጡን!
ታሪክ የሰሩትን በደል ሲደርስባቸው ከጎናቸው መሆን ካልቻልን ሌላ ታሪክ ሰሪ መፍጠር አንችልም!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Wednesday, May 4, 2016

በኢትዮጵያ በሕግ ሽፋን የዜጎችን መብት መጣስ ተባብሶ መቀጠሉን ሂውማን ራይት ሊግ አስታወቀ

ኢሳት ዜና :- ኢትዮጵያ ውስጥ የፀረ ሽብር ሕግን ከለላ በማድረግ መብታቸውን የሚጠይቁ ዜጎችን ማሰር፣ መግደልና ኢሰብዓዊ ድርጊቶችን መፈጸም ተጠናክሮ መቀጠሉን የምስራቅ አፍሪካ የሰብዓዊ መብት ሊግ ገልጿል። ድርጅቱ በኦሮሚያ ክልል የበርካታ ንጹሃንን ሕይወት የቀጠፈው ዘግናኝ እልቂት በህወሃት ኢህአዴግ መራሹ ገዥ ቡድን የተቀነባበረ መሆኑን አስታውቋል።
ይህን ኢሰብዓዊ እልቂት ተቃውመው ለመብታቸው የታገሉት ከ 22 በላይ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች የሃሰት ክስ እንደተመሰረተባቸው አመልክቶ ፣ በህወሃት የተቀነባበረ ሴራ በሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ካለ ፍትሕ በእስር ቤት እየማቀቁ ነው ብሎአል።
በኢትዮጵያ ያለው የፀረ ሽብር ሕግ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችን በሚጻረር መልኩ የወጣ ሲሆን ይህም የዜጎችን የመጻፍ፣ የመናገርና የመቃወም ሕገ መንግስታዊ መብቶችን በሚጥስ መልኩ ሆን ተብሎ ተረቆ በሥራ ላይ መዋሉን አስታውቋል።
በኦሮሚያ የተነሳውን ሰላማዊ የዜጎችን ጥያቄ በመደገፍ ከሕዝባቸው ጋር በመሆን ሲቃወሙ ከነበሩት ውስጥ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ፣ የፓርቲው ፀሃፊ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አዲሱ አቡላና ሌሎችም በፈጠራ የሽብር ክስ መከሰሳቸውንና የመብት ጥሰቱ ተባብሶ መቀጠሉን ሪፖርቱ አመላክቷል።
መብታቸውን በመጠየቃቸው ብቻ በሽብር ሕግ ስም አላግባብ ታስረው የሚገኙ ንጹሃን ኢትዮዮጵያዊያንን ህወሃት መራሹ መንግስት ካለ ምንም ቅድመ ሁኔታዎች ክሳቸውን በማንሳት ሊፈታቸው ይገባል ብሎአል።

10421433_648203905313009_8566024657772797199_n

ሰበር መረጃ ወያኔ በሀገ ወጥ ሰዉ ዝዉዉር ሰንሰለት ዉስጥ !

Gudish Weyane's photo.
የኢኳዶር ፖሊስ ( Ecuadorean police ) የኮሎምቢያ የጸረ አጋች ቡድን ወይም ኽዉላ ( Colombia’s elite anti-kidnapping squad, known as GAULA ) የአሜሪካዉ ሆም ላንድ ሴኪዉሪቲ ( us Home land security ) የብራዚል የህገ ወጥ ሰዉ ዝውውር ቁጥጥር ፖሊስ ( Brazilian migration police ) እና የሩቅ ምስራቅ ሀገራት ፖሊስ መረጃዎች እንዲሁም አለማቀፍ ፖሊስ ( Interpol ) በመተባበር የህገ ወጥ የሰዉ ዝዉዉርን ለማኮላሸት በጋራ መስራት ከጀመሩ ሰንበትበት ብለዋል!