Translate

Friday, February 13, 2015

ለጨካኝ ስርአት የጨከነ ትግል

የኢትዮጵያ ህዝብ በህውሃት ስራአት የደረሰበትን መዘርዘር ብዙ ቢሆንም ለህልውናችን ፀር የሆነው የወያኔ ስራአት ፍጹም በሚሰቀጥጥ ሁኔታ ህዝባችንን ያለማቋረጥ እያሰቃየ ይገኛል::Protest in front of TPLF embassy in Washington DC
በ 23 አመት የግፍ አገዛዙ የመጨረሻው ምእራፍ ላይ የደረሰው ወያኔ እንደ ከዚህ ቀደሙ በግፍ መቀጠል የማይችልበት፣ የኢትዮጵያ ህዝብም የሚገዛበት የባርነት መሸከሚያ ትከሻው እየተሰባበረ ያለበት፤ ወያኔን ወልደው ያሳደጉት እና ያሰማሩት ባእዳን ሃገሮችም የመቀጠል ሀይሉን ለክተውት፣የኢትዮጵያ ህዝብንም የአልገዛም ባይነት መንፈሱን ተረድተውት ወያኔን እያጣጣሉት ይገኛሉ፡፡ ወያኔም የመጨረሻ የጣር በትሩን አንስቶ ገና በእናቱ ሆድ ያለን ፅንስ በግፍ ዱላ እያፈርሰ፣ ታዳጊ ህጻናትን ከራሱ አልፎ በባእዳን እያስገደለ ይገኛል።
የኢትዮጵያ መጥፋት ለወያኔ ትንሳኤ ሲሆን፤ የወያኔ ስርአት መወገድ ደግሞ ለኢትዮጵያዊያን ትንሳኤ ነው። በመሆኑም ህውሃት አርባኛ አመቱን ለማክበር በሚሊዮኖች ብር መድቦ በመከራ ላይ ባለው ወገናችን የካቲት 11 ከበሮ ሲደልቅ እኛም በውጭ የምንገኝ ህውሃት የተፈጠረበትን እለት በክፉ ቀን ማስታወሻነት በከረረ ተቃውሞ በወያኔ ኢንባሲ ፊት ለፊት እናሳልፋለን:: እርሶም በስፍራው ጥቁር ልብስ በመልበስ ይህ መርገምት የሆነው ወያኔ የተፈጠረበትን ቀን በአንድላይ ሆነን በተቃውሞ እንድናሳልፍ እንጠይቃለን።
ቦታ፦ Embassy Of Ethiopia 3506 International Dr NW Washington,DC.20008
ቀን፦ እሮብ Feb 18, 2015
ሰአት፦ 9:00 AM
ለበለጠ መረጃ፦ dcjointtaskforce@gmail.com ወይም 571 403 2474

No comments:

Post a Comment