Translate

Wednesday, June 29, 2016

“የአማራና የኦሮሞ ምሁራን መነጋገር አለባቸው” – ጀዋር መሐመድ አዲስ ቃለምልልስ ከሕብር ራድዮ ጋር

<…በኦሮሚያ ክልል የተፈጸመውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚቃወምና የድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ ወደፊት ተጽዕኖ የሚያሳድር የሕግ ረቂቅ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ንዑስ ኮሚቴ በሁለቱም ፓርቲ አባላት ሙሉ ድጋፍተቀብሎት ለሴኔቱ ተመርቷል ።ይህ ሕግ ሆኖ ሲወታ የአሜሪካና የሕወሓትን ግንኙነት ይለውጣል። ይህ እንዲሆን ግን የተደረገው ስትራቴጂ..በእርግጠኝነት የምናገረው በወልቃይት፣በቅማንት ፣ለሱዳን በተሰጠው መሬት ሳቢአ የተገደሉት ንጹሃን ቁጥር በኦሮሚያ ተቃውሞውን ተከትሎ ከተገደሉት በእጥፍ ይበልታል።ይህን ግን ተከታትሎ በኦሮሚያ እንደተደረገው የእያንዳንዱ ሟች ብቻ ሳይሆን በተለይ የአካባቢው ፖሊስም ሆነ ልዩ ሔኢል በግድያ ሲሳተፍ የገዳዩ ማንነት ጭምር ቢወታ ኖሮ ከኦሮሚአው ጋር አንድ ላይ ማቀናጀት ይቻል ነበር ግን ያ አልሆነም። በአማራ የተፈጸመውን ግድያ ተከታትሎ የዘገበው የለም። ስራ አልተሰራም ይሄ ቢሰራ ኖሮ…> ጃዋር መሐመድ የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ዳይሬክተር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከሰጠን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)
ጃዋር
የአማራና የኦሮሞ ምሁራን መነጋገር አለባቸው ይላል
ሕዝቡ ለሺህ ዓመት አብሮ የኖረ አንዱ ከአንዱ ጋር የተሳሰረ የአንዱ ችግር ሌላውን የሚመለከተው ነው
የረቂቁን ወደ ሴኔት ማለፍ ተከትሎ የዌአኔ ባለስልታናት አሁንም የጀመሩትን ሩጫ አጠናክረው ይቀጥላሉ እና ሌሎችንም ሀሳቦች በቃለ መጠይቁ ተካተዋል።

በአ.አ. 17 የፖሊስ አባላትና 1 የወረዳ ባለስልጣን ተገደሉ – መንግስት የሞተው 1 ፖሊስና 1 ባለስልጣን ብቻ ነው እያለ ነው

(ዘ-ሐበሻ) በመላው ኢትዮጵያ ገዢው የሕወሓት መንግስት ሕዝብን በየፊናው እያሰቃየ ባለበት በአሁኑ ወቅት ሕዝብ የራሱን እርምጃ በባለስልጣናቱና ጠመንጃን በታጠቁ ሰዎች ላይ መወሰድ ጀምሯል:: ዛሬ በአዲስ አበባ የነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 17 የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት እና አንድ የወረዳ ከፍተኛ ባለስልጣን መገደላቸው ታውቋል::
በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ በተለምዶው ሃና ማርያም አካባቢ የሕዝብን ቤት ለማፍረስ የተያዘውን እቅድ ለማስፈጸም የከተማው አስተዳደር ከሕዝቡ ጋር በተፋጠጠበት ወቅት ከሕወሓት ደህንነት ቢሮ የተላኩ ሰምቶ አደሮች ባነሱት ግርግር የተነሳ; ተነሳ በተባለው ግጭት ፖሊሶች ወደ ህዝብ መተኮስ በመጀመራቸው ህዝቡ የራሱን እርምጃ በመውሰድ በ17 የፖሊስ አባላት እና በወረዳው ባለስልጣን ላይ እርምጃ ወስዷል::

ከህዝቡም ወገን በርካታ ሰዎች እንደቆሰሉ የተሰማ ሲሆን ፖሊሶችም እንዲሁ እንደተጎዱ መረጃው ይጠቁማል::
ይህንን ብጥብጥ ህዝብ እንደጀመረው ለማስመስል የደህንነት አባላቱ ተንኩሰው መሰወራቸውን የሚናገሩት የአይን እማኞች ሆን ብሎ ቤቴ አይፈርስብኝም ያለውን ህዝብ ለማሸማቀቅ ነው ብለዋል::
ይህ በ እንዲህ እንዳለ መንግስት በዛሬው ብጥብጥ 1 ፖሊስ እና አንድ የወረዳ ባለስልጣን መገደሉን ገልጾ ጥቃቱን ሕገወጦች ያደረሱት ሲል ወንጅሏል:

Tuesday, June 28, 2016

“የትግራይ ሰዎች ተፈናቀሉ” አጉል የወያኔ ጩኸት በሽንፋ – ጎንደር

ሊቁ  እጅጉ እና አዳነ አጣናው
ላለፉት 40 ዓመታት አገርን  በማፈራረስ አባዜ  የተጠመደው  ወያኔ  በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ምክንያቶችን  በመፍጠር  ሲፈልግ  የትግራይ  ሕዝብ  ልጆቹን  ስለሰዋ  የትግራይ  ግዛት መስፋት አለበት፣ በሌላ  ጊዜ ደግሞ አባላቶቹን  አደራጅቶ  በተለያዩ   የሀገሪቱ  ክፍሎች በማስፈር፣ ብሎም  ከባንክ ብድር  በገፍ እንዲያገኙ በማድረግ  በሰፈሩባችቸው  አካባቢዎች ሁሉ  የንግድና  የእርሻ ሥራዎችን  በበላይነት እንዲይዙ አድርጓል። ስለሆነም  ወያኔዎች ተደራጂተው በሰፈሩባችው አካባቢዎች  ሁሉ  የአካባቢው ተወላጅ  በራሱ ቀዬ የበይ  ተመልካች  እንዲሆን  ተደርጓል ። በአጭሩ  ወያኔዎች ለ25 ዓመታት በመላ  ሀገሪቱ  የሚያካሂዱት  ዘረፋና የማያባራ የግዛት ተስፋፊነት ሌላው ቀርቶ በራሳቸው አምሳል የፈጠሯቸው  አጫፋሪ  የጎሣ  ድርጅቶች  እንኳ  ገደብ  የለሹን የወያኔ  ሁሉም  የኔ ይሁን በሽታ  ሥራ ላይ ለመትግበር ከአቅማቸው በላይ እየሆነ መጥቷል።
“<በጅብ  ጅማት  የተሰራ ክራር  ዜማው ሁልጊዜም  እንብላው> እንደሚባለው  ወያኔ ዛሬም እንዳመሰራረቱ ታላቋን  ትግራይ  የመፍጠር  በሽታው በተጠናከረ  መልኩ  ቀጥሏል። ወያኔ በጠባብነት ታዉሮ  አትዮጵያን  በስፋትና በአኩልነት ሊመራ  ቀርቶ እወክለዉ አለሁ የሚለውን  ትግራይን  እንኳ በአግባቡ በእኩልነት መወከል የተሳነው  የአንድ  አካባቢ ስብስብ  ነው፡፡. ለይስሙላ የትግራይ  ሕዝብ  ወኪል  ነኝ  ቢልም  እውነቱ  ግን በበላይነት እና በዋናነት የሚመራው  ከአርባ ዓመት በፊት አሽአ ማለትም አድዋ፣ ሽሬ፣ አክሱም ብሎ የመገንጠል ዓላማ አንግቦ  በሕቡእ  የተደራጀው ከሦስት አውራጃዎች በመጡ እጅግ በጣም ጠባብ  ግለሰቦች ሲሆን  ከኢትዮጵያ ጎሳዎች ያልተቀላቀልን  ‘ንጹሕ ትግሬ  እኛ  ነን የሚሉ በዝምድና  እና በጋብቻ የተሣሰሩ የአውራጃ አንጀኞች ናቸው።

Wednesday, June 22, 2016

ሰበር ዜና… እስከ አፍናጫቸዉ የታጠቁ ከ20 እስከ 25 ሺ የሚጠጉ የአርበኞች ግንቦት7 እና የትህዴን ወታደሮች በጾረና ግንባር ነበሩ

በልኡል አለም

Patriotic Ginbot7 attacked TPLF troopsበህወሃት አመራር እና በሰሜኑ እዝ ዉስጥ በሚገኙ የወታደራዊ ደህንነት መረጃ ክንፎች በተለይም ወታደራዊ እግረኛ ቃኘዉ መረጃ፣ የቴሌስኮፕ ምልከታ ቃኘዉ መረጃ፣ የሬዲዮ ጠለፋ አገልግሎት መረጃ፣ የሳተላይት ቅኝት መረጃ፣ የአስተኳሽ አስተላለፍ መረጃ፣ የመግቢያና መዉጫ ኮድ ሚስጥር አሳላፊ አመራር መረጃ ምድቦች ባጠቃላይ ወደ ግምገማ እንዲገቡ ከመከላከያ ሚኒስቴር ቀጥታ ትእዛዝ ቢተላለፍም የወታደራዊ ደህንነቱ አጣብቂኝ ዉስጥ መግባቱን ታማኝ ምንጮች ጠቅሰዋል።

ህወሃት “አምባሳደሮችን” በታማኞቹ ሊተካ ነው!

“የማይታመኑ ከሆነ [አለመታመናቸውን] ማሳየት አለባቸው”

ambassadors

በተለያዩ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በወሳኝ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ እንደሆነ ተነገረ፡፡ በህወሃት ውስጥ ያለው ፍርሃቻና አለመረጋጋት ለሁኔታው አስገዳጅነት ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡ ህወሃት ለዓመታት ያገለገሉትን ሎሌዎች የማያምናቸው ከሆነ እነርሱም “አለመታመናቸውን” ማሳየት ይገባቸዋል፡፡

Wednesday, June 15, 2016

ኤርትራውያን ጥላችን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሳይሆን ከወያኔ ጋር ነው አሉ

(ECADF)— ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ሕወሃት) ሰኔ 7 ቀን 2008 በጾረና ግምባር ወደ ኤርትራ ግዛት ተንቀሳቅሶ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ የኤርትራ ኢንፎርሜሽን ሚኒስቴር ባወጣው አጭር መግለጫ “የሕወሃት አገዛዝ በፆረና ማዕከላዊ ግንባር ጦርነት ከፍቶብናል” ነበር ያለው።Eritrea says the TPLF Regime launches an attack
የኤርትራ መንግስት “ኢትዮጵያ ጥቃት ፈጸመችብኝ” አለማለቱ ኤርትራውያን የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘረኛና አምባገነን አፋኝ ሥርዓት ስር ደፍጥጦ እየገዛ ያለው በሕዝብ ያልተመረጠና ከአንድ አነስተኛ የህዝብ ብዛት ካለው ብሄር የወጣ እራሱን የብሄረሰቡ ነጻ አውጪ እያለ የሚጠራ አናሳ ቡድን ሕወሃት እንደሆነ በሚገባ ስለሚያውቅ ነው።

የህወሀት ወንጀለኞች ያልተመዘገበ ቦንድ ባሜሪካ ሲሸጡ ማጅራቸዉን ተያዙ!

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
T-TPLF Criminals Nabbed in America Selling Unregistered Bonds!
ባለፈው ሳምንት የዩኤስ አሜሪካ የቦንድ እና አክስዮን ልውውጥ  ኮሚሽን/U.S Securities and Exchange Commission (SEC) በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው የሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ (ዘ-ህወሀት) ለአራት ዓመታት ያልተመዘገበ ህገ ወጥ የቦንድ ሽያጭ በማካሄድ ያገኘውን 6.5 ሚሊዮን ዶላር እንዲመልስ  (ዲስጎርጅመንት ወይም በትክክል ስተርጎም “ማስተፋት”)  ቅ ጣት  በይኖበታል ።