Translate

Wednesday, March 30, 2016

ህወሃት ራሱን በራሱ ሸንጎ አስገምግሞ የእጁን ደም ሊያጸዳ ነው

የኮሚሽኑ ሪፖርት በኢህአዴግ ጽ/ቤት መሰራቱ ተጠቆመ

ehrc
ህወሃት በኦሮሚያና በአማራ ክልል በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈጸመውን ወንጀልና ርህራሄ አልባ ግፍ ራሱ አጣርቶ፣ ራሱ አጠናክሮ፣ ራሱ በፈጠረው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አማካይነት አቅርቦ፣ በራሱ ሸንጎ በማጸደቅ እጁን ከደም ሊያጸዳ ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ይፋ መሆኑንን ተከትሎ ለሪፖርቱ ማዳመቂያ የምስል ቪዲዮዎች መዘጋጀታቸው ታወቀ

እነዚህን ከስር የምትመለከቷቸውን ፎቶዎች ወዳጆቼ ከባህር ዳር ዛሬ ሌሊት ላኩልኝ።

ኣማራ ሲሞት ሌላ ኣማራ ሲፈራ ( ሄኖክ የሺጥላ )
እነዚህን ከስር የምትመለከቷቸውን ፎቶዎች ወዳጆቼ ከባህር ዳር ዛሬ ሌሊት ላኩልኝ።



ስለ ፎቶዎቹ ምንነት ባጭሩ ላስቀምጥ
ተደብዳቢው -- አማራ!
ደብዳቢው--- ወያኔ ትግሬ!
የድብደባው ምክንያት--- አማራ መሆን!
ተጠያቂ ---የለም!!!
ይህንን ለማስቆም የሚቆም አማራ--- የለም!!!
ይህንን ኣይቶ ቁጭት ውስጥ ሊገባ የሚችል አማራ--- የለም!!!
ድብደባው ይቀጥላል ወይ?---- ኣዋ!
ይህንን ፎቶ ለብዙ ደቂቃ ተመለከትኩት ። ኣይኖቼ እንባ ተሞልተው ጥርሴን እያፋጨሁ ደግሜ ደጋግሜ ኣየሁት። ወዳጄ በውስጥ መስመር የፃፈልኝን ኣሳዛኝ ታሪክም ኣነበብኩ ። ማልቀስ ኣልችልም ፥ ኣሁንም ያለቀስኩ ኣይመስለኝም ፥ ግን ፊቴ ላይ እንባ የሚመስል ነገር እንደነበር ኣስታውሳለሁ ። መናደድም ኣልፈልግም ፥ ምክንያቱም ከመናደድ የሚመጣው ሽንፈት እንደሆነም ኣውቃለሁ ። ግን ማሰብ እፈልጋለሁ ፥ ድጋሚ ወደ ራሴ ተመልሼ እውነታውን በጥሞና ማየት እና መረዳት እፈልጋለሁ ። 

ኢትዮጵያ ወዴት ነው የምትሄደው እና የማትሄደው? (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
(እ.ኤ.አ መጋቢት 27/2016 በማሪዮት ጆርጅታዎን  ከተማ  (ዋሺንንግቶን ድሲ ) ቪዥን ኢትዮጵያ በተባለው ድርጅት አስተባባሪነት “ስለወደፊቷ ኢትዮጵያ፡ ሽግግር፣ ዴሞክራሲ እና ብሄራዊ አንድነት ጉባኤ” በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛው ቅጅ ከቀረበው ንግግር የተወሰደ ነው፡፡)
Quo Vadis Ethiopia: Where Are You (not) Going?
“ስለወዲፊቷ ኢትዮጵያ፡ ሽግግር፣ ዴሞክራሲ እና ብሄራዊ አንድነት ጉባኤ” በሚል ርዕስ ስለተዘጋጀው ጉባኤ ቪዥን ኢትዮጵያን እና የጉባኤውን አስተባባሪዎች በሙሉ ለማመስገን እፈልጋለሁ፡፡
ፕሮፌሰር ጌታቸው በጋሻው ከወራት በፊት በዚህ ጉባኤ ላይ እንድገኝ እና እንድሳተፍ ጥሪ ባቀረበልኝ ጊዜ ኢትዮጵያን ገጥመዋት ባሉት መሰረተ ሰፊ የተሳትፎ መድረክ፣ ውይይት እና ክርክር ጉዳዮች ሀሳብ እጅግ በጣም ነበር የተደሰትኩት፡፡ የቪዥን ኢትዮጵያን አርዓያ በመከተል ሌሎችም እንደዘሁ በርካታ የውይይት መድረኮችን ያዘጋጃሉ የሚል ተስፋ አለኝ፡፡

አንድ ሰሞን ከሙኒኮች ጋር (በኤፍሬም ማዴቦ)

በኤፍሬም ማዴቦ
አባባ . . .  አባባ . . . . ስማ አባባ ረሳህ እንዴ አለኝ ያ ባለፈዉ ነኃሴ ወር ስንለያይ ያስለቀሰኝ ልጄ።  ምኑን አልኩት።  ቅድም ምሳ ላይ የነገርኩህን . . . እንዴ!  እሱንማ እንዴት እረሳለሁ። Please don’t አባባ! …… I will not! ሲረጋጋና ደስ ሲለዉ ታየኝና ልቤን ደስ አለው። ልጄ ኮሌጅ የሚገባበት ቀን እኔ ደግሞ ከትግል ጓደኞቼ ጋር የምንገናኝበት ቀን ናፍቆናል። አባባ Good luck አለኝ። እኔም ይቅናህ አልኩት። Good luck እና ይቅናህ የተባባልነው እኔ እሱ የሚመኘዉ ኮሌጅ እንዲገባ እሱ ደግሞ እኔ በድል ኢትዮጵያ እንድገባ ነበር። ሁለታችንም ይቅናን . . . አሜን!!!
አዉሮፕላን ዉስጥ ገብቼ ከተረጋጋሁ በኋላ ኢር ፎኑን ጆሮዬ ውስጥ ሰክቼ አይፎኔ ላይ “Play” የሚለዉን ስጫነዉ ጥላሁን ገሰሰ “አራዊቱ ሁሉ መጥቶ ቢከበኝ” እያለ ጀመረኝ። የምወደው ዘፈን ነበርና ደጋገምኩት። ጥላሁንኮ ድምጻዊ ብቻ አይደለም ነቢይም ነዉ፤ የዛሬ ስንትና ስንት አመት በአራዊቶች እንደምንከበብ ተንብዮ ነበር። የሚቀጥለው ዘፈን ገና ሲጀምር ምን መሆኑ ታወቀኝና. . . . . ኧረ በፍጹም. . . እንዴት ተደርጎ አልኩና አይፎኔን ዘግቼዉ ኪሴ ዉስጥ ከተትኩት። “መለያየት ሞት ነዉ” የሚለዉን የጥላሁን ገሰሰ ሙዚቃ ብወደዉም የጠነከረዉ ሆዴ እንዲባባ በፍጹም አልፈለኩም። አይፓዴን አወጣሁና የአስናቀች ወርቁን ሰዉነት እየሰረሰር ገብቶ አንጀት የሚያርስ ክራር መኮምኮም ጀመርኩ። አስናቀች ኢትዮጵያን ጨምሮ ብዙ ቦታ ወሰደችኝ፤ ደግነቱ ዬትም ትዉሰደኝ ዬት መልሳ መላልሳ እዚያዉ አዉሮፕላኑ ውስጥ ታመጣኝ ነበር . . .  አለዚያማ!

ፈርዖናዊው የወያኔ አገዛዝ በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ሲደገም ምን ይመስላል?

ከወልቃይት ጠገዴ ብጌምድር፤ ጎንደር  ኢትዮጵያ
በ24 አመታት ውስጥ በተለያዩ የኢትዮጵያ አከባቢ ጥቂት የሚባሉ መልካም ለውጦች ቢኖሩም እንኳ ጀግናው የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ አይደለም የመልካሙን ለውጥ ሊያጣጥም እንዲያውም በተቀነባበረ ሁኔታ የዛሬ 24 አመት ከነበረበት የህልውናና  ኑሮ ብዙ እጥፍ አሽቆልቁሎ ተምዘግዝጎ ወርዶበታል፤ ወያኔ አሰቃይቶታል፤ ህይወቱና አኗኗሩ አመሰቃቅሎበታል፤ ለብዙ መከራና ስቃይ ሞትና እንግልት መታሰርና ደብዛ መጥፋት መሰደድና መሸማቀቅ ዳርጎታል። የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከ1972 ጀምሮ የወያኔ መርዝ የተርከፈከፈበት ህዝብ ነው። አሳዛኙ ነገር ወያኔ የፈጠረው ችግር በሁሉም የኢትዮጵያ መርዙን ከመትፋቱ ጋር ተያይዞ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ወገኑ የየራሱን ህመም ሲያዳምጥ ስለኖረ ከህመም ሁሉ ህመም፣ ከእልቂት ሁሉ እልቂት ሲፈጸምበት፣ በእስራኤላውያን ላይ በኦሽዊትስ ካምፕ በናዚዎች የተቀነባበረው የዘር ማጥፋት በ21ኛው መ.ክ.ዘ በወያኔዎቹ በግልጽና በድብቅ ሲደገም የሚዲያ ሽፋን ስለማይደርሰው ኢትዮጵያዉያን ወገኖቹ ሊያውቁለትና ሃይ ሊሉት አልቻሉም መከራዉን ከ1972 አ/ም ጀምሮ ወገኖቹ ሳይደርሱለት ብቻውን ሲጎነጭ ኖሯል።
እዚህ ላይ ለማሳሰብ እምፈልገው ዋና ነጥብ  በአማራነታችን እየደረሰብን ያለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ ህወሃት በመልካም አስተዳደር ስም ለማስተባበል መሞከር በፍጹም አይቻልም፤   የመልካም አስተዳደር ችግርማ አሜሪካም ውስጥ ቢሆን ይኖር ይሆናል። እኛ አንደላቃችሁ አኑሩን አይደለም እያልን ያለነው። ዋናው ጥያቄያችን የወልቃይት ጠገዴ ህዝብና መሬት አማራ ስለሆነ ወደ እናት አገራችን ወደ ጎንደር ወደ አማራነታችን መልሱን የሚል ነው። ሰላምን ፈልገው ከመለሱን እጅግ ደስ ይለናል ካልሆነ ደግሞ የእነርሱ ፈቃድና ምስክርነት ሳያስፈልገን በራሳችን ራሳችንን አማራነታችንን አስረግጠን እንመልሳለን።በቃ ይሔው ነው!!! ይህ በትግራይ ተስፋፊና ነጻ አውጭ ቡድን፣ በትግራይ ፖሊስ፣ በትግራይ ልዩ ሃይል፣ በአጋዚ ወታደር፣ በትግራይ አስተዳደር አመራሮችና ካድሬዎች ማዳፈን የማይቻል የሚፋጅ ረመጥ ጥያቄ ነው።

Tuesday, March 22, 2016

ኃይለማርያም ቋፍ ላይ የደረሱ ይመስላሉ!

“…እኔ ምን አባቴ ላድርግ…” አሉ

hailemariam


አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሰሞኑን የሚሰጡት አስተያየትና ንግግር ህወሃት/ኢህአዴግ ያፈጠጠበትን ችግር ብቻ ሳይሆን እርሳቸውም በቋፍ ላይ የደረሱ መሆናቸውን ያመላከተ እየሆነ ሄዷል፡፡ ወደ ሥልጣን ሲመጡ በሙስና ላይ ዘመቻ እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ይናገሩ የነበሩት ኃይለማርያም እስካሁን የሚታይ ለውጥ ሳያመጡ ቀርተዋል፡፡ በቅርቡ ከምሁራን ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይም “የተለያየ አመለካከትን የማይቀበል ሥርዓት የጊዜ ጉዳይ እንጂ መውደቁ አይቀርም” ማለታቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ችግሩን በቀጥታ ከኢህአዴግ ጋር እያያዙ በግልጽ መናገራቸው በሕይወታቸው ላይ አደጋ እስከሚያመጣ የደረሰ መሆኑ ለጎልጉል የደረሱ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በመሆኑም የግል ጠባቂዎቻቸውና አጃቢዎቻቸው ላይ የተደረጉ ለውጦችን ከዚህም ጋር የሚያያይዙ ወገኖች ኃይለማርያም በእርግጥም በችግር ውስጥ እንዳሉ ጠቋሚ መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ የዚያኑ ያህልም ኃይለማርያም የናሙና ወይም ተወካይ መሪ ስለሆኑና መዘውሩ በእጃቸው ስለሌለ በእርግጥም “እኔ ምናባቴ ላድርግ” ማለታቸው ይህንኑ የሚያሳይ ነው ይላሉ፡፡

ሰሜን ጎንደር ውጥረቱ ከሯል:: ሕወሓት ራሱ በፈጠረው የጎሳ ፖለቲካ ውጤት ዲቃላውን ብኣዴንን እየወነጀለ ነው::

ሕወሓት ራሱ በፈጠረው የጎሳ ፖለቲካ ውጤት ዲቃላውን ብኣዴንን እየወነጀለ ነው::
ሰሜን ጎንደር ውጥረቱ ከሯል::12243233_1699617866976076_4679020848657870642_n
12243233_1699617866976076_4679020848657870642_nሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ብሎ ራሱን የሚጠራው እና ታላቋን ትግራይ በመስፋፋት ካልመሰረትኩ ነጻ አውጪ የሚለውን ስሜን አልቀይርም በማለት በአማራ እና በአፋር ክልሎች የመስፋፋት እቅዱን ለመተግበር ሲሮጥ ከፍተኛ የሆነ እንቅፋት ከአማራው ሕዝብ ስለተጋረደበት ራሱ የፈጠረውን ዲቃላውን ኢሕዴን/ብኣዴንን መወንጀል መጀመሩ ከሕወሓት የገደል ማሚቱዎች የተገኙ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው::ሕወሓት ፊቱን ወደ ተላላኪዎቹ አዙሩ በምትካቸው ከሕወሓት ጉያ የተመለመሉ አማርኛ ተናጋሪ ሕወሓቶችን ለመተካት እየሮጠ ይገኛል::በሰሜን ጎንደር ተፈጥሮ የሚገኘው ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ አመጽ ወደ ግጭት የተቀየር ሲሆን ከጎንደር ከተማ ጀምሮ እስከ ዳንሻ ድረስ ሕዝቡ አስፈላጊውን የሕይወት መስዋትነት ለመክፈል ጥርሱን ነክሶ መሰሳቱ ታይቷል::