Translate

Monday, March 25, 2013

Current Petition Saudi Police Torture of Innocent Ethiopians


Current Petition

Saudi Police Torture of Innocent Ethiopians

  • For residents of Ethiopia, please enter ETH in the Zip/Postal Code form field.
  • Residents of other countries with No Zip/Postal Code, please enter NONE in the form field.
  • Only Form fiels with a red * are required fields
  • SMNE will not share your email or any other information you entrust to us.
  • ህዝበ ክርስቲያንን ያሳዘነ ሥልጣን በእግዚአብሔር ቤት መቅሰፍት ነዉ! ከዉርደትና ዉድቀት ሌላ የሚያመጣዉ ተስፋ የለም!


    በአጥቃዉ ቦጋለ

    በቅድስት አገራችን ኢትዮጵያ የሃይማኖት ነጻነት ከአደጋ ላይ ወድቋል። ታሪካዊትና ቀደምት  ቤተክርስቲያናችን  ዉስጥ በሃይል ገብቶ የመሸገዉ የገዥዉ ቡድን ለዘመናት በኖሩ የሃይማኖት እምነቶች ላይ የሃይል ዘመቻ ከፍቷል፤ የአማኙን ህዝበ  ሰላም  ነስቷል። የእርቀ ፤ የሰላምና አንድነት መድረክ ተዘግቶ ከምዕመናን ፍላጎት ዉጭ የታካሄደዉ የካድሬዎች የሃይማኖት መሪ  ሹመት እጅግ አሳሳቢ ሁኗል። መንግስት በጥንታዊታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ እጁን አስገብቶ እየፈጸመ ያለዉን ህገ ወጥ ድርጊት በጥብቅ እንቃወማለን።
    በሃይማኖት አባቶች አማካይነት የሰላምና አንድነት ጉባኤ ለሶስት ተከታታይ አመታት  ፓትርያሪክ በህይዎት እያለ ቀኖና ተጥሶ በመንግስት ጣልጋ ገብነትና አስገዳጅነት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዮስን አዉርዶ የተካሄደዉን  ህገወጥ ሹመት በእርቅ መፍትሄ ለመፈለግ የተጀመረዉን የሽምግልና ሂደት የወያኔዉ ቡድን አሰናክሎ እንደተለመደዉ በዘር ያዘጋጃቸዉን  የካድሬ አባት ሹሟል።  ይህንን ከንቱ የጥፋት ሹመት ህዝበ ክርስቲያን ከአሁን በፊትም በአባትነት አልተቀበለም አሁንም አይቀበለዉም።

    ነብር ዥንጉርጉርነቱን “ግራ ዘመም” ኢትዮጲያዊ ክሽፈቱን


    ነብር ዥንጉርጉርነቱን “ግራ ዘመም” ኢትዮጲያዊ ክሽፈቱን

    በክፍሉ ሁሴን
    ታምራት ነገራ በፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”መጽሃፍ ላይ የሰጠውን አስተያዬት ካነበብኩትProfessor Mesfin Woldemariam is one of Ethiopia's well-known intellectuals በኋላ የመጣብኝ ሃሳብ ሰውዬው የሚለውን ያውቀዋልን? የሚል ነው። እንደምፀት ሆኖ አሁን በማላስታውሰው ምክንያት ግን በወቅቱ በወደድኩለት አንድ የፌስቡክ አስተያዬቱ ብዙም በአንባቢነትና አለማቀፍ ነገሮችን በመተንተን ችሎታው የማላማው ይልቁንም የእሱን አይነት ሃይማኖት ያላቸውን ሰዎች “የአዲስ ኪዳን በግ ቅዱስ ካህን፤ የፅድቅ ንጉስ የአለም መድህን” እያልኩ የምመሰጥበት ሌላ ጓደኛዬ በዚያው እኔ የታምራትን አስተያዬት “ላይክ” ማድረግ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም የፌስቡክ ባልንጀሮቼ ባቃመስኩበት ወቅት “ይህ ታምራት የሚለውን ያውቀዋልን?”ሲል የጠየቀውን አስታወሰኝ። ምናልባት ጌታን በተቀበለና ባልተቀበለ መካከል ያለ ልዩነት ይሆን?

    የቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች በርሃብ ተጎድተው ወደ ሆስፒታል እየተወሰዱ ነው


    ከመጋቢት 2 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በትምህርት ማቆም አድማ ላይ የነበሩት የኢትዮጵያ ኦርቶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ስላሴ መንፈሰሳዊ ኮሌጅ ደቀመዛሙርት በርሃብ ተጎድተው ወደ ሆስፒታል እየተወሰዱ እንደሆነ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ገለፁ፡፡

    “እኔ ግን አልሞትኩም” – አላሙዲ


    ‹‹ጠ/ሚ/ር መለስን በማጣቱ ሰው ተደናግጦ ነበር፤ … እኔንም ገለውኝ ነበር፤ ግን አልሞትኩም እስከአሁን ከእናንተው ጋር ነኝ›› ሲሉ መናገራቸውን ሼክ ሙሐመድ ሁሴን አል-አሙዲ መናገራቸውን ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው ኢትዮቻናል ጋዜጣ ዘገበ። ዘገባው ለግንዛቤ ይጠቅማል በሚል ሳንጨምር ሳንቀንስ አቅርበነዋል – ያንብቡት። በአሁኑ ወቅት በሥሩ 20 ግዙፍ ኩባኒያዎችን የሚያስተዳድረው የሜድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ባለፈው እሁድ 10ኛውን የደምበኞች፣ የሠራተኞችና የቤተሰቦች ቀን በዓል አከበረ፡፡ የቴክኖሎጂ ግሩፑ ቺፍ ኤግዚክዩቲቭ ኦፊሰር ዶ/ር አረጋ ይርዳው በበዓሉ ላይ እንደገለፁት ‹‹የሜድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ውስጥ መሪዎችም ሆንን ተመሪዎች ሁላችንም እኔንም ጨምሮ ሠራተኞች ነን፤ አሠሪ ቢኖር አንድ ሰው ብቻ ነው›› ነበር ያሉት፡ ፡ ዶ/ር አረጋ ‹‹ አንድ አሠሪ ብቻ ነው ያለን›› ያሏቸው ክቡር ዶ/ር ሼክ አል- አሙዲ በበዓሉ ላይ ባደረጉት ንግግርም ‹‹ለአንድ ሀገር መመስረቻው ቤተሰብ ነው፡ ፡ ከዚያ ቀጥሎ ቤተሰብ ወልዶ ተዋልዶ ሠራተኛ ይፈጥራል፤ ሠራተኛውም ለሚያመርተውም ደምበኛ ያመጣል፡፡ ከምወዳቸው ነገሮችና መገኘት የምፈልገው ይህንን ቀን ነው›› ብለዋል፡፡

    ! …….. “ኣሸባሪ” ነኝ ………..!

    By Abraha Desta 

    ! …….. “ኣሸባሪ” ነኝ ………..!

    ትናንት በሰሩት ነገር ገርሞኝ ወድያ ወዲህ ስል ስለ ህወሓት ጉባኤ መረጃ ኣላሰባሰብኩም ነበር። ወደ ማታ ኣከባቢ በማላውቀው ስልክ ተደወለልኝ። ከተወሰነ ሰጣገባ በኋላ “ኣንተ ኣሸባሪ ነህ። በኣሸባሪነት እንደምንትያዝ ኣትጠራጠር” ኣለኝ።

    “ኣዎ ኣሸባሪ ነኝ። ያሸበርኳቹ ያህል ነው የሚሰማኝ። ምክንያቱም ባላሸብራቹ ኑሮ የኔን ፌስቡክ ለማስዘጋት ባልተረባረባቹ ነበር” መለስኩለት።

    ስልኩን ጀሮየ ላይ ጥርቅም ኣድርጎ ዘጋው።

    “ለካ እንዲህ ለነፃነት የሚቆሙ፣ የፈለጉትን የሚፅፉ፣ ስለ ፍትሕ የሚዘምሩ ግለሰዎች ናቸው ‘ኣሸባሪ’ ተብለው በኣምባገነን ገዢዎች የሚሰየሙት” ስል ኣሰላሰልኩ። “ኣሸባሪ” የሚለውን ስም ወድጀዋለሁ። “ኣሸባሪ” መሆን ደስ ይላል። ጥያቄው መሆን ያለበት ‘የሚሸበረው ኣካል ማነው?’ (ሰለማዊ ህዝብ ወይስ ገዢው መደብ) ነው። ምናልባት እኔ “ኣሸባሪ” ከተባልኩ በኔ የተሸበረው ገዢው ፓርቲ ብቻ ነው።

    ግን ገዢው መደብ የሚያሸብሩ ሰዎች ሌላ ስም ሊሰጣቸው ይገባል እላለሁ። ምክንያቱም መሪዎቻችን ስልጣናቸውን ያለ ኣግባብ ተጠቅመው ሰለማዊ ህዝብ ሲያሸብሩ ምን ብለን ልንሰይማቸው ነው? መንግስትን የሚቃወም “ኣሸባሪ” ከተባለ፣ ህዝብን በጭቆና የሚያሸብር ባለስልጣንስ ????

    ከጭቆና በላይ ሽብር የለም። ምክንያቱም ጭቆና ማስፈራራት፣ ግድያ ……… ምናምን (ሰው ፈርቶና ተሸብሮ ሳይቃወም እንዲገዛ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶች የሽብር ተግባራት ናቸው)። “ሽብር” ማለት’ኮ ኣንድ ኣካል ራሱ የሚፈልገውን ተግባር በሌሎች ሃይል በመጠቀም ወይ በማስፈራራት ለመጫን ሲሞክር ነው። ሌሎችን እያስፈራራ ያለው ማነው??? እኔ ወይስ ገዢው ፓርቲ? ኣሸባሪ ማነው? ማነው ሰለማዊ ዜጎችን በማፈን እያሸበረ ያለው?

    በቆብ ላይ ሚዶ ትምህርትና ተማሪ ቤት


    በቆብ ላይ ሚዶ ትምህርትና ተማሪ ቤት

    (ክፍል አንድ)
    ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም
    ጥር 2005
    በአለፉት አርባ ዓመታት ውስጥ አንድ ልብ ያላልነው መሠረታዊ ለውጥ አለ፤ እንዲያውም የመከራችን ሁሉ ምንጭ ነው ለማለት ይቻላል፤ የመሪዎቻችን አለመማር ብቻ ሳይሆን ትምህርትን መናቅ ወይምProfessor Mesfin Woldemariam is one of Ethiopia's well-known intellectuals ጭራሹኑ መጥላት ዋና ባሕርያቸው ሆነ፤ እስከደርግ ዘመን የነበሩት የአገር መሪዎች ቢያንስ የአንደኛ ደረጃውን (ዳዊት መድገም) የአገሩን ባህላዊ ትምህርት ያከናወኑ ነበሩ፤ ከዚያ በኋላ ለጨዋ ቤተሰብ ልጆች ትምህርት ማለት በቤተ መንግሥት በመዋል የሚገኝ ልምድ ነበር፤ ተፈሪ መኮንን በአሥራ ሦስት ዓመቱ ደጃዝማች የሆነውና ሥልጣን ላይ የወጣው በመወለድ ያገኘውን ዕድል በልምድ እንዲያዳብረው ነበር፤ ተክለ ሐዋርያት ከአሥር ዓመታት በላይ ሩስያ ተምሮ ሲመለስ ተፈሪ ያገኘውን አላገኘም።