Translate

Tuesday, November 12, 2013

ወያኔ ማለት ቁምጣ ለብሶ የመጣ ደርግ ነው ፡፡

http://www.facebook.com/photo.php?v=286230021510610
ጥቁር ሽብር ወያኔ ቁምጣ የለበሰ ደርግ ነው ! እመኑኝ በየትኛውም የታሪክ ገጠመኝ የሳወዲ መንግስት የዚህ አይነት ድፍረት ያውም በአደባባይ በዜጎቻችን ላይ አሳይቶ አያውቅም ፡፡ ነገሮችን ተመልሰን ከተመለከትን ይህ ግፍና በደል የእኛው ባለስልጣናት ሳውዲወችን አደፋፍረው ያስፈፀሙት ጉዳይ ነው፡፡

Monday, November 11, 2013

የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል!

በኃይሉ አርአያ (ዶ/ር) - የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት አባል

ሰሞኑን የኢሕአዴግ መንግሥት ይፈራል አይፈራም የሚል ጉዳይ ከፓርላማ ተነስቶ ወደ መገናኛ ብዙኃንም ደርሷል። ጉዳዩ
 የተነሳው የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ አዲሱ ፕሬዚዳንታችን በፓርላማ ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ

ባቀረቧቸው የማማሻሻያ ሐሳቦችና ጠቅላይ ሚኒስትራችን በሰጡት ምላሽ ዙሪያ ነው። ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዝ ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት 13 ቀን 2006 ዓም በአወጣው ዕትሙ ‹‹'ፈሪ' መንግሥት?›› በሚል ርዕስ ጋዜጠኛ የማነ ናግሽ ጥሩ ትንተና አቅርቧል። የፍርኃት ነገር ከተነሳ ጋዜጠኛው ያነሳውን ለማዳበር በእኔም በኩል የምለው አለኝ። የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል። የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል ስል ግን በደፈናው አይደለም። በርካታ የማይፈራቸው ነገሮች አሉ። ለምሳሌ ጦርነትን አይፈራም። በተለይ ሕወሓት/ኢሕአዴግ ጥርሱን ነቅሎ ያደገበት ጉዳይ ነው። ሕግ መጣስን አይፈራም። ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን መጣስን አይፈራም። መዋሸትን አይፈራም።

የኢሕአዴግ መንግሥት ይፈራል ስል በተለይ የማተኩረው በአንድ ጉዳይ ላይ ነው። እውነት ላይ። የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን ይፈራል። እውነትን ስለሚፈራ እሱ ራሱ በሚፈልገው መንገድ እንዲታወቅ ከሚፈልገው ውጪ ሕዝቡ እውነቱን እንዲያውቅ አይፈልግም። ይህ ደግሞ የአምባገነን አውራ ፓርቲዎች መንግሥታት አንዱና ዋናው የደባቂነትና የሸማቂነት መገለጫ ባህሪ ነው። የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን ለመፍራቱ በርካታ ማስረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል። ለጊዜው ግን አራቱን ብቻ በምሳሌነት እንደሚከተለው ልጥቀስ።

Friday, November 8, 2013

ሕወሓት አለማቀፍ አሸባሪ መዝገብ ላይ በአሸባሪነት የሚታወቅበት ፕሮፋይል::

ምንጭ :- START – UNIVERSITY OF MARYLAND – የአሸባሪዎች አጥኚ ቡድን
የአሸባሪ ድርጅቶች መዝገብ
በሃገሩ ቋንቛ መጠሪያው .. አልተገለጸም
የድርጅቱ ስም …..የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (TPLF)
የሚንቀሳቀስበት አከባቢ … ኢትዮጵያ
የተቋቋመበት ጊዜ ….. አልተገለጸም
የአባላቶቹ ቁጥር/ጥንካሬው … አይታወቅም
መለያው ….. ኮሚኒስት/ሶሻሊስት/ብሄርተኛ/ተገንጣይ
የገንዘብ ምንጩ …. አይታወቅም
የተነሳበት የፖለቲካ ፍልስፍና
ራሱን የትግራይ ንቅናቄ ወይንም ወያኔ በማለት በ1970ዎቹ መጀመሪያ በመንግስቱ ሃይለማርያም አገዛዝ ላይ የተጀመረ ተቃውሞበ1975 አከባቢ የትግራይ ነጻ አውጪ በማለት ተመስርቶ በኤርትራ ነጻ አውጪ ስር እየተዳደረ ውጊያ የከፈተ ድርጅትነው::አላማቸው የአልቤንያን ሞዴል የተከተለ የኮሚኒስት ስርኣት በማስፈን የታለመ…የትግራይን ህዝብ ከደርግ አገዛዝ ነጻ ለማውጣትየተነሳ ነበር::በሜይ 1989 የደርግን ሰራዊት በማሸነፍ ሙሉ ትግራይን መቆጣጠር ችሎ ነበር::በተለያየ ጊዜ ከሻእቢያ ጋር እና በተናጠልበተለያዩ አከባቢዎች የአሸባሪነት ድርጊት ፈጽሟል::

Breaking news የግንቦት 7 መሪዎችን ለመግደል የተጠነሰሰው ሴራ ከሸፈ

xx
በኢትዮጵያ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ዋና ሃለፊ በአቶ ጌታቸው አሰፋ እና በጠቅላይ ሚኒስትሩ የብራዊ ደህንነት አማካሪ በአቶ ጸጋየ በርሄ ቁጥጥር የተመራና በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌና በግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል መሪዎች ላይ የተቀነባበረው የግድያ ሙከራ ከሸፈ።
ከግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንዳመለከተው ለግድያ የተላከው ሙሉቀን መስፍን የተባለው ግለሰብ በትናንትናው እለት በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን፣ በእየደረጃው ከሚገኙ የደህንነት ሀላፊዎች ጋር በስልክ ሲያደርግ የነበረው የስልክ ለውውጥ በህዝባዊ ሀይሉ የመረጃ ክፍል ሲቀዳ ቆይቷል።
ወያኔ-ኦ-ሚሊኒየም በሚል የተመራው የግድያ ዘመቻ -በነገው እለት ጥቅምት 30/2006 ዓም ሊካሄድ ታቅዶ እንደነበር የድምጽ መረጃው ያመለክታል።

ትግል በመሰዋትነት ይሰፈራል!!!

ከተስፋዬ ዘበነ(ኖርዌይ በርገን)

ሃገርና ሕዝብ በውጥረት በታመሰበት አምባገነን የህውሃት/ኢአዴግ/ ዘረኛ ስርዓት ከምስራቅ እስከ ምህራብ ከሰሜን እስከ ደቡብ ሃገሪቱን እንደ ብራና ወጥሮ የሕዝቡን ኑሮ ሲያከብድበት እያየንና እየተመለከትን ስርኣቱን ለመታገል በየትኛውም መልኩ የተዋቀርን ድርጅቶች ሳንጀምር እየጨረስን ወይም እራሳችን ስላዋቀርነው ፓርቲ፣ ድርጅት ወይም ሸንጎ ሳንመረምር ሌሎች ስለሚደክሙበትና ስለሚለፉበት ትግል መፃዪ እድል እየተነበይን እርስ በእርስ ስንናከስና ስንጣረዝ የዘረኛውን የህውሃት እድሜ አበርክተን እዚህ አድርሰነዋል፡፡
በዚህ እኩይ የህውሃት ስርዓት መጀመሪያ ጀምሮ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል በራስ ተነሳሺነት ተዋቅረው እየተንቀሳቀሱ ያሉት የፖለቲካ ድርጅቶች አላማና ግባቸውን ለማስፈፀም የሰላማዊ ትግል መርሆችን ተግባራዊ ለማደረግ አንድም በራሳቸው የውስጥ ችግር ምክንያት፣ በዋነኝነት ግን ስርዓቱ ካለው ተፈጥሮዊ ባህሪ አንፃር ከሕዝብ ጋር ያለው ትስስርና በሕዝብ ላይ የሚፈፅመው የመልካም አስተዳደር ችግርም ሆነ የሰብሃዊ መብት አያያዝ እንዲሁም ሌሎች ዘርፈ ብዙ ችግሮች ስላሉበት በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለተደራጁ  ፓርቲዎች  ነፃነት ሰጥቶ ሞቱን ማፋጠን አይፈልግም፡፡

Thursday, November 7, 2013

ኢትዮጵያ፣ የቦምብ ፍንዳታ እና ማስጠንቀቂያው

ኢትዮጵያ ውስጥ የሽብር ጥቃቶች ሊደርሱ ይችላሉ በሚል የጸጥታ ኃይሎች በተጠንቀቅ እንዲቆሙ በታዘዙበት በኣሁኑ ወቅት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኣንድ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ላይ በፈነዳ ቦምብ አራት ሰዎች መሞታቸው ተዘገበ።
ከሶስት ሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ላዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አዲስ ኣበባ ላይ ከናይጄሪያው ቡድን ጋር በሚጫወትበት ዕለት ጥቃት ለማድረስ ሲዘጋጁ ነበር የተባሉ ሁለት የሶማሊያ ኣጥፍቶ ጠፊዎች በራሳቸው ቦምብ መሞታቸው ይታወሳል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ህብረተሰቡም ጥንቃቄ እንዲያደርግ መንግስት እያሳሰበ ሲሆን የጥንቃቄ ማስጠንቀቂያውን ተከትሎም በተለያዩ አካባቢዎች የጸጥታ ቁጥጥሩ መጠናከሩም ተሰምቷል።

አብዮት እና ወጣትነት – በወጣት ሃብታሙ አያሌው (የአንድነት ፓርቲ ም/የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ)

ክፍል 1
ሰሞነኛ
አዲሱን አመት ተቀብለን ሁለት ወራት ሳንሻገር ጥቅምት 11 ቀን የኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ እና ሥራ አሥኪያጁ ጋዜጠኛ ሚሊዮን ደግነው ክስ ተመስርቶባቸው ፍርድ ቤት ቀረቡ፤ በዳግም ቀጠሮ ዕረቡ ጥቅምት 20 ቀን በሐዋሳ ከተማ ጋዜጠኞቹ ለፍርድ ቤት ቀጠሮ ሄደው በስልት የተቀናበረ በሚመስል ሆኔታ ለመኪና አደጋ ተዳርገው ጋዜጠኛ ኤፍሬም የከፋ አደጋ ሲደርስበት ዋና አዘጋጁ ጌታቸው እና ሥራ አስኪያጁ ጋዜጠኛ ሚሊዮን በመለስተኛ ጉዳት መትረፋቸው ተሰማ፤ ጥቅምት 13 ቀን እኔን ጨምሮ ሌሎች ሦስት ጓዶቼ አንድ አመት በተጓተተ ክስ ፍርድ ቤት ቀርበን ክሱ ለህዳር 24 ተቀጠረ፡፡
ጥቅምት 15 ቀን የኢትዮጵያ ህዝብ አብዝቶ የሚሳሳለት ጋዜጣኛ ተመስገን ደዳለኝ ፍርድ ቤት ቀርቦ አንደ ገና በድጋሚ ቀጠሮ ጠቅምት 21 ውሎው ፍርድ ቤት ሆነ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስተር ኃይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው መንግስታዊ ስልጣናቸውን በመጠቀም በሀሣብና በአመለካከት ጎራ ለይተው በሚታገሏቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ፍረጃ አና ዛቻ ሲሰነዝሩ ከረሙ፤ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ቤተ መንግስቱን ለቅቀው በየወሩ ግማሽ ሚሊዮን ወደ እሚከፈልበት ቤታቸው ሲያመሩ ዶ/ር ሙላቱ ፕሬዘዳንት የሚል ስያሜ በመያዝ ሰተት ብለው ወደ ቤተ መንግስቱ መግባታቸው ተሰማ፡፡