Translate

Thursday, November 7, 2013

ሀገራዊ ውርደት እንዲያበቃ ወያኔን ከሥልጣን ማስወገድ!!!

የወያኔ ገዢ ጉጅሌ በባህርዩ ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት አጋጥሟት የማያውቅ ፍጹም ኢሰብዓዊና ነውረኛ ስብስብ እንደሆነ ለመረዳት ኢትዮጵያዊያንን ለማዋረድ የሚጠቀሟቸውን ተግባራትና ቃላትን ማጤን ይበቃል።
በሶማሌ ክልል የኦብነግን ታጣቂዎች ቅስም ለመስበር ልጃገረዶችንና እናቶችን ብቻ ሳይሆን ወንዶችንም ጭምር በቤተሰብ ፊት በደቦ የሚደፍሩ፤ ለዚህ ተግባር የሠለጠኑ የልዩ ጦር አባላት መኖራቸው በስፋት የሚታወቅና በተደጋጋሚም የተዘገበ ጉዳይ ነው። ወያኔ፣ የኦጋዴን ወገኖቻችን በዚህ ጥቃት ተሸማቀው ያነገቡትን መሣሪያ ጥለው ፀጥ-ለጥ ብለው ይገዛሉ ብሎ ተስፋ ያደረገ ቢሆንም እየሆነ ያለው ግን የዚህ ተቃራኒ ነው። ዛሬ የሶማሌ ክልል ወንዱም ሴቱም፤ ወጣቱም አዛውንቱም በፀረ-ወያኔ አቋም የጋራ መግባባት ላይ ደርሷል። በኦጋዴን የወያኔ አስነዋሪ ጥቃት የፈጠረው ምሬት በውጭ አገራትም በሚደረጉ የፀረ ወያኔ ትግሎች የኢትዮጵያ ሶማሌ ተወላጆች ተሳትፎ እንዲጎለብት አድርጎታል። በሶማሌ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት በሁላችንም ላይ የደረሰ ነውና ቁጭታቸውን እንጋራለን። በሶማሌ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት ሀገራዊ ውርደት ነው።

Wednesday, November 6, 2013

ህወሓት አይድንም፤ እያቃሰተ ነው (አስገደ ገብረስላሴ ከመቀሌ)

 ‹‹የህ.ወ.ሓ.ት  ትንሳኤ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ድላችን የማይቀር ነው ›› ስብሓት ነጋ
Belgu Kasa's photo.     በጌታቸዉ  አረጋዊ  የህ.ወ.ሓ.ት ኣባልና የድምፅ ወያነ ጋዜጠኛ  «ውራይና » የሚል በትግርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ለአራተኛ ጊዜ በነሃሴ ወር 2005 ዓ/ም የታተመ መፅሄት ስብሓት ነጋ  የህ.ወ.ሓ.ት   ፈላስፋ ቃለ መጠይቅ ያደረገበት መፅሄት በፅሞና  ኣነበብኩት። የመፅሄቱ ዋና ይዘት   ‹‹ህ.ወ.ሓ.ት እናድናት›› ነዉ የሚለዉ ስብሓት ነጋ በመፅሄቱ የተካተቱ ብዙ ስንክሳራዊ  ሃተታ ተናግሯል ።
  • አሁን ማለት የፈለግኩት በመፅሄቱ የተካተቱ በሙሉ መልስ ለመስጠት አይደለም፡፡ ምክንያቱም የስብሓትን ስንክሳር መልስ ለመስጠት  ከፈለኩ ግዜ አይገኝም  መፅሃፍም  ሊሆን የሚችል ነዉ። በመሆኑም አለፍ አለፍ በማለት  የስብሓትን አንኳር አንኳር ነጥቦች መልስ ለመስጠት እሞክራለሁ።
   ሌላ ይህ ፅሁፍ መልስ ለመስጠት የተገደድኩት የ ህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች ለትግርኛ ቋንቋ  ማዳበርን  በትግርኛ ስነ-ፅሁፍ ለማስፋት ብለዉ በፅሁፍ ቢናገሩ እጅጉን የሚደገፍና የትግራይ ህዝብ መስዋእት ነበር። ይህ ደግሞ ማንም ኢትዮጵያዊ  ይድግፈዋል፤፤

አይ አበሻ! አበሻና ሆድ፤ አንድ (ፕ/መስፍን ወልደ ማርያም)

ወያኔና የነፖሊቲካ አጋሮቹ የሚያደርጉትን ለእነሱ የሚመች አከፋፈል ትተን አበሻን ለሁለት እንክፈለው፤ ሆድ ያለውና ሆድ የሌለው፤ ወይም የሚበላና የማይበላ፤ ዛሬ የምናገረው ሆድ ስላለው ወይም ስለሚበላው አበሻ ነው፤ አታውቁት እንደሆነ ተዋወቁት፤ በአጠቃላይ ስንመለከተው ግን የአበሻ ፍቅርም ሆነ ጠብ ለሆድ ነው፤ አበሻን የሚያጣላው፣ የሚያነታርከው፣ የሚያቧጭቀው የሆድ ነገር ነው፤ ለመብላት ነው፤ አንዳንዴም ሎሌውን ለማብላት ነው፤ ግብር ለማግባት ነው።
አዳም አበሻ ሳይሆን አይቀርም፤ ሁሉንም ነገር ብላ ከተከለከለው በቀር ብሎ ያስቀመጠው ይመስላል፤በላባችሁ ወዝ ብሉ ተብለው አዳምና ሔዋን መረገማቸውን አበሻ ገና አልሰማም፤ አበሻ የተፈጠረው ገነት ውስጥ ቁጭ ብለህ ያለውን ሁሉ ብላ በተባለበት ጊዜ ነው፤ እግዚአብሔር አበሻን ሁሉንም ብላ ሲለው ምናልባትም በጆሮው ጭራሽ አታስብ ብሎት ይሆናል፤ እስቲ በመጀመሪያ ስለምግብ እንነጋገር።

Tuesday, November 5, 2013

የፖለቲካው ስር ቁማርተኞች! (ተመስገን ደሳለኝ)

Journalist Temasegan Dasalegበሀገራችን መንግስታዊ አስተዳደር የ‹‹ቁማር ህግ››ን ችግር መፍቻ አድርጎ መጠቀም የጀመረበትን ጊዜ ለማስላት ንጉሰ ነገስት ዳግማዊ ምንሊክ እንደ”ተበሉበት” ከሚነግረን የሽኩሹክታ ታሪካችን አንስቶ አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት… እያልን ለመቁጠር እንገደዳለን፡፡ ይሁንና ባለሙያ (በንባብ የደረጀ) ቁማርተኛ ፖለቲከኛ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛበት ድንገቴ ክስተት የ1966ቱ አብዮት ዋዜማ ነው ቢባል ወደ እውነታው ይጠጋል፡፡ ከመንግስቱ ኃ/ማሪያም ‹‹ለምሳ ያሰቡንን፣ ቁርስ አደረግናቸው›› እና የአጥናፉ አባተ ፍፃሜን ጨምሮ የእነተስፋዬ ደበሳይና ብርሃነ መስቀል ረዳ፤ የእነኃይሌ ፊዳና አለሙ አበበ፤ የእነሌንጮ ለታና ባሮ ቱምሳ፤ የእነ አባይ ፀሀዬና አረጋዊ በርሄ፤ የእነታምራት ላይኔና ያሬድ ጥበቡ… ከትግል መድረክ መገለል ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ባለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት ደግሞ በእነመለስ ዜናዊና ስዬ አብርሃ፤ በእነኃይሉ ሻውልና ቀኝ አዝማች ነቅዐ ጥበብ፤ በእነብርሃኑ ነጋና ልደቱ አያሌው፤ በእነመረራ ጉዲናና አልማዝ ሰይፉ፤ በእነግዛቸውና ያዕቆብ ኃ/ማርያም… መካከል የተፈጠሩ የሃሳብ ልዩነቶች የተፈቱበት መንገድ በዚሁ የጨዋታ ህግ የተስተናገደ መሆኑን የሚያሳዩ በርካታ ተጨባጭ ሁነቶች አሉ፡፡ እነዚህ ልዩነቶች የተቋጩት ከመተዳደሪያ ደንብ ውጪ፣ የተሻለ ዕድል ያለውን ካርታ ቀድሞ በመዘዘ ብልጣ ብልጥ አሸናፊነት ነው፡፡ በዚህ ፅሁፍ የምናየው ‹መልክአ ቁማር›ም ከእንዲህ አይነቱ የጥሎ ማለፉ ጨዋታ በተጨማሪ የመንፈስ ልዕልናቸውን ያረከሱትንም የሚያካትት ይሆናል፡፡

የትኛውን‹‹አሸባሪ›› እንጠቁማችሁ?

ትናንትና ኢቲቪ ‹‹የእኛ ጉዳይ›› ብሎ ስለ አልሻባብ ውይይት አቅርቧል፡፡ በእርግጥ እነ ኃ/ማሪያም ለገንዘብ ማግኛም ይሁን ለኢህአዴጋዊ ጀብድ በየ መድረኩ ‹‹አልሻባብ ተንኮታኩቷል›› ከሚሉት በተቃራኒ አልሻብብ አሁንም አስፈሪ፣ ስራ አጥነት መቅረፍ የግድ መሆኑን፣…..ሌላም ሌላም ከኢቲቪ የተለዩ የሚመስሉ ሀሳቦች በተወያዮቹ ተነስተዋል፡፡ እውን እነ ኃ/ማሪያም ከሰሙ ‹‹የአሸባሪዎች ስልታቸው እንጅ ጥያቄያቸው ተገቢ (ሌጅቲሜት) ነው››ም ተብሏል፡፡ ነገሩ ተወያዮቹ ከነ ሽመልስ፣ በረከት፣ ኃ/ማሪያም እንደሚሉዩ ማየት የሚቻለው ስለ ኢትዮጵያ ‹‹ሽብርተኛ›› ብዙም አለማለታቸው ነው፡፡
ሆኖም በስተመጨረሻ ‹‹ሽብርን ለመግታት አስቀድሞ መረጃ ስለመስጠት፣ ከፖሊስ ጋር ስለመስራት….›› የተሰጠው ማሳሰቢያ ከእነ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ጉትጎታ ጋር የው ተመሳሳይ ነው፡፡ ምክንያቱም የኮሚኒቲ ፖሊስ፣ ደህንነትም ሆነ ሌሎቹ ‹‹አሸባሪ›› ብለው መረጃ አሰባሰብን ብለው ያሰሯቸው ኢትዮጵያውያን ፈንጅ ለማፈንዳት ይቅርና ፈንጅ እንኳን በእጃቸው ነክተው የማያውቁ ናቸው፡፡ እስክንድር ነጋ የታሰረው ፌስ ቡክ ላይ እየጻፈ በነበረበት ወቅት ነው፡፡ ርዕዮት አለሙ አሸባሪ ተብላ የተያዘችው ‹‹በቃ!›› በሚል አዲስ አበባ ውስጥ የተለጠፈን ጽሁፍ ፎቶ ስታነሳ በመገኘቷ መሆኑን ሰምቻለሁ፡፡ አቡበክርና ሌሎች የኮሚቴው አባላት፣ ውብሸት ታዬ፣ በቀለ ገርባ…… ይልቅ የኢህአዴግ ታጋይና ካድሬዎች ለፈንጅና ሽብር ቅርቦች ናቸው፡፡

Monday, November 4, 2013

ግንቦት 7 አድባር ትከተልህ!

ይሄይስ አእምሮ

ምን ብዬ ከየት እንደምጀምር አላውቅም፡፡ ሁሉም ነገር ተምታትቶብኛል፡፡ መፈጠሬ ራሱም አስጠልቶኛል፡፡
ግንቦት ሰባት ሆይ! እንደሰውም እንደድርጅትም ልብ ብለህ ስማኝ! በቃ፤ በቃ ማለት በቃ ነው፡፡ ከሰሞነኛ አንድ ኢትዮጵያዊ ውርደት በኋላ አቋሜን ሙሉ በሙሉ ለውጫለሁ፡፡ እናም በስሜት ግንቦት ሰባት ሆኛለሁ፤ በተግባርም እሆናለሁ፡፡ ያበጠው ይፈንዳ፡፡ ማንም በኔ አያገባውም፡፡ ግንቦት ሰባት የማይሆንን ተቋምም ይሁን ግለሰብ አወግዛለሁ – የማወግዘው የኔም የቤተሰቤም ውርደት እንዲቀጥል ፈቃደኛ መሆኑን ከመገንዘብ አኳያ ነው፡፡ በወጡ ሳይወጠወጥ የሥልጣን ጥማቸውን የውይይት መድረክ ላይ ፊጥ የሚያደርጉ ዜጎች ከአሁን በኋላ አንደበት የላቸውም፡፡ መድረክ ላይ መደስኮር ሌላ ነው – እኛ ያለንበትን መከራና ስቃይ ማጤን ደግሞ ሌላ ነው፡፡

“ኧረ እኔስ ጨነቀኝ”

“ኧረ እኔስ ጨነቀኝ”

(ርዕሰ አንቀጽ)
worried


ሰውየው ያገባት ሚስቱ ቤተሰቦቿ ሃብታሞች ነበሩ። እሱ ደግሞ መናጢ የሚባል ደሃ ነበር። አንድ ቀን የማይቀረው ሞት የሚስቱን አባት ነጠቀና ቀብር ወጡ። አስከሬን እየተከተሉ ሲያለቅሱ ባል ሚስቱ ጎን ሆኖ ልክ እንደሷ “አባቴ አባቴ” በማለት ያለቅስ ጀመር። ሚስትም ” የት የወለደህን ነው አባቴ የምትለው” በማለት አፍታ ወስዳ ባሏን ገሰጸችው።