Translate

Monday, November 4, 2013

የሀይሉ አማራጭ፣ የኤርትራ ድጋፍና ተቃውሞው

ከዳኮታ ጥናት መአከል

የኛ ነግር መልሶ መላልሶ ሆኗል። በገራችን አቆጣጠር በ1960ዎቹ የተማሩና የነቁ ወጣቶች አቢዮት ማካሄድ በጀመሩ ጊዜ የተነሱ ልዩነቶች አንዳንዴ ቅርጻቸውን በመጠኑ ይቀይሩ ይሆናል እንጂ ዛሬም ድረስ ባንድ ወይ በሌላ በኩል  የልዩነትና የፍዳችን ምንጭ ሆነው ቀጥለዋል። እነዚህ ልዩነቶች  መረቀቂያዎች፤ መጣያያዎች ቢያመች መገዳዳያዎቻችን ናቸው።   ችግር የሆነው ጎራ ለይተው በነበሩ ፖለቲከኛች  የሀሳብ ልዩነቶቹ መፈጠራቸው ወይ መኖራቸው አልነበረም። ወይ ልዩነት የተፈጠሩባቸው አገራዊ ቁም ነገሮች ስህተተኛነትና ወይ አላስፈላጊነት ኖራቸው አይደለም። ትናንትናም ሆነ ዛሬ ምንአልባትም ነገም ችግር የሚሆነው  ምንም አይነት ልዩነት ላይ በረጋ ሁኔታ መነጋገር፤ ልዩነትን ማቻቻል፤ አብሮ የሚያሰራና በጋራ የሚያታግል  ማድረግ አለመቻሉ ነው። በሚያሳዝን ሁኔታ ይህ ችግር ከአርባ አመታት በሗላም ያሳየው  መሻሻል እዚህ ግባ የማይባል ነው። ዛሬም ድረስ ቡድንም ሆነ ግለሰብ ልዩነት ታየበት ማለት አለቀ ጠላት አድርገው የሚፈርጁ ፖለቲከኞችና ድርጅቶች በገፍ አሉን። ያኔ ትግሉን በዋናናት የመሩትና ፖለቲካውን የተወኑት ዛሬም ወሳኔ ሰጪዎች በሆኑበት እዚህ ችግር ውስጥ መዳከራችን ብዙም አይገርምም።

በህወሃት ውስጥ የዕርቅ ሃሳብ መነሳቱ ተሰማ

"የኢህአዴግ የአፈና ገመድ ነትቧል፣ ድርጅቱ ተናግቷል"

tplf1


ኢትዮጵያ ግራ በሚያጋባና ሊተነበይ በማይችል የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ መገኘቷን ያመኑ የህወሃት ሰዎች መካካል የእርቅ ሃሳብ ላይ ለማተኮር እቅድ እንዲያዝ ሃሳብ ማንሳታቸው ተሰማ። ኢህአዴግ የቀድሞው የአፈና ገመዱ መንተቡን የሚያሳዩ ምልክቶች መታየታቸውና አለመተማመን መንገሱ ተጠቆመ።

Sunday, November 3, 2013

ብሄራዊ ጭቆናን የማስወገድ ትግሉ ለአንድ ብሄር (ወይ ግለሰብ) የሚተው የግል ስራ አይደለም። Abraha Desta

ኢትዮዽያውያን ዘረኞች አይደለንም፤ በዘር አልተለያየንም። ኢትዮዽያ ዉስጥ የተለያየ ዘር የለም። ዘራችን አንድ ነው፤ የሚለያየው ቋንቋችን ነው። የተለያየ ቋንቋ (ና እምነት) አለን። የተለያየ ቋንቋ መኖር ደግሞ ባህሪያዊ ነው። የተለያየ ቋንቋ መኖር በራሱ ችግር አይደለም። 
የኢትዮዽያውያን ችግር ብሄር (ቋንቋ) ሳይሆን ፖለቲካ ነው። የሚያጣላን ቋንቋችን ሳይሆን ለስልጣንና ሃብት ያለን ስስት ነው። የችግሩ መንስኤ የስልጣን ፍላጎታችን ብቻ አይደለም፤ የህዝባችን ፖለቲካዊ ንቃተ ህሊና ማነስ ጭምር እንጂ። ስልጣን ፈላጊዎች (ፖለቲከኞች) የፈለጉትን ለማግኘት ህዝብን መቀሰቀስ አለባቸው። በተወሰነ መልኩ ህዝብን ለመቀስቀስ ስሜቱን መንካት አለብህ። ስሜቱ ለመንካት ከሌላው የሚለይበት ነገር እያነሳህ “እኛና እነሱ” የሚል ክፍፍል መፍጠር ግድ ይላል (በምክንያታዊነት ለማያምን ህዝብ)። 

ሕዝባዊ መሰረት ያለው ፓርቲ ህዝቡን አይሰልልም!

የመብራት መጥፋት ዋናው ችግር የ”ጠባቂነት” ባህል ነው!
የኤሌክትሪክ ኃይል በየግቢያችን ልናመነጭ ነው!
እውነቱን ልንገራችሁ አይደል—-ያሳለፍነው ሳምንት የአግራሞት ነው፡፡ የአሜሪካንን የስልክ ጠለፋና የስለላ ጦስ ሰማችሁልኝ አይደል? እንዴ — አንድዬን ብቻ እኮ ነው ያልሰለለችው! (የሚጠለፍ ስልክ የለማ!) እኔማ ምን እንደመሰለኝ ታውቃላችሁ? በቃ — በልጅነቴ እሰማው የነበረው 8ኛው ሺ የገባ ነው የመሰለኝ፡፡ እስቲ አስቡት—የጀርመኗ ቻንስለር አንጌላ መርከል፤ለአስር ዓመት ስልካቸው እየተጠለፈ ተሰልለዋል፡፡ እሺ— መሪዎቹስ እርስ በእርስ ይተዋወቁ ይሆናል፡፡

Saturday, November 2, 2013

“ከ6 ሚሊዮን የኢህአዴግ አባል አንዱ ብሆን ምን ችግር አለው;” አቶ ልደቱ አያሌው

CC
አቶ ልደቱ አያሌው
“ከ6 ሚሊዮን የኢህአዴግ አባል አንዱ ብሆን ምን ችግር አለው;”
አቶ ልደቱ አያሌው
“ወ/ት ብርቱካን የተሰጣት ኃላፊነት አግባብ አይደለም”
“እንባ አውጥቼ አልቅሼ ኃላፊነት በቃኝ እያልኩ ነው የተመረጥኩት”
“ከኢንጂነር ኃይሉ እንዲሕ ያለ ውሸት አልጠብቅም ነበር”

Hiber Radio: “እነሱ ለዓላማቸው ፈንጂ መርገጣቸውን ሲነግሩን ነበር እኛ ደግሞ የእነሱን እስርና ድብደባ ፈርተን ወደ ኋላ አንልም..” – አቶ ሃብታሙ አያሌው (ቃለ-ምልልስ)

“እነሱ ለዓላማቸው ፈንጂ መርገጣቸውን ሲነግሩን ነበር እኛ ደግሞ የእነሱን እስርና ድብደባ ፈርተን ወደ ኋላ አንልም..”
አቶ ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ም/የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ለህብር ከሰጡት ቃለ ምልልስ
ህብር ሬዲዮ በወቅቱ በአገር ቤት በገዢው ፓርቲ የደህንነት አባላት የጥቃት ዒላማ ስለሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባላትና አንዳንድ አመራሮች ጉዳይ ከአቶ ሀብታሙ አያሌው የፓርቲው ም/የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ተወያይተናል።
አቶ ሀብታሙ በዛቻ ወንጀል ፍ/ቤት እየተመላለሱ ነው። ለምን? የደህንነት አባላት ሶስት የፓርቲው የተለያዩ አመራሮችን እያፈኑ ወስደው እደበደቡ አስፈራርተዋል። ቀጣዩ እርምጃ ምን ይሆናል በዚህ መንገድስ የአንድነት ቀጣይ እርምጃ ይቆማል የሚሉና ሌሎችም ሀሳቦች ዙሪያ ተወያያተናል። በውጭ ለሚኖረው ኢትዮጵያዊም ወጣቱ ፖለቲከኛ አቶ ሀብታሙ አያሌው መልዕክት አላቸው። ሙሉውን ያዳምጡ:-

“ልጆቼም እኔም ፍትህ እንሻለን”

saa

(የሟች ኢ/ር ጀሚል ባለቤት፤ ወ/ሮ ፋጡ የሱፍ)
“ለመጀመሪያ ጊዜ የባሌን መታመም በስልክ ነው የሰማሁት፡፡ ሌላ ጊዜ ወገቡን ያመው ስለነበር ያው ህመሙ ነበር የመሰለኝ። ተኝቷል ወደተባለበት አሚን ጀነራል ሆስፒታል በፍጥነት ስሄድ ያጋጠመኝ ሌላ ታሪክ ነው፡፡ ባለቤቴ ጭንቅላቱ ተጐድቷል፤ አንድ የቀረ የሰውነት ክፍል የለውም፡፡ ተደብድቧል፡፡ ራሱን ስቶ እየቃዠ ነበር ያገኘሁት (… ከፍተኛ ለቅሶ …) ነገሩን ሳጣራ በብዙ ሰዎች ተደብድቦ ከቡታጅራ ነው ወደ አሚን ጀነራል ሆስፒታል የመጣው”
ይሄን የተናገሩት ግንቦት 20 ቀን 2004 ዓ.ም የ“ሊቃ” በዓልን ለማክበር ወደ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ፣ ሚኬኤሎ ገበሬ ማህበር፣ መልካሜ መስጊድ፣ ከጓደኞቻቸው ጋር ሄደው፣ ባደረሰባቸው ድብደባ ህይወታቸው ያለፈው የኢ/ር ጀሚል ሀሰን ባለቤት ወይዘሮ ፋጡማ የሱፍ ናቸው፡፡