Translate

Friday, November 2, 2012

በትንሹ ሰባሁለት ኢትዩጵያዊያን ስደተኞ ሞቱ ተባለ


ኢሳት ዜና:-በትንሹ  72  ኢትዩጵያዊያን  ስደተኞች  ከሶማሊያ  ቦሳሶ  ወደብ  ወደ የመን  ለመግባት ሲሞክሩ  ባህር ውስጥ  ሰጥመዋል  ሲሉ  የየመን  ባለስልጣኖች አስታወቁ ።

የተወሰኑ  የ ኢትዮጵያውያኑን  አስከሬን  በፎቶ  አስደግፎ  የተሰራጨው  ይሕ ዘገባ  እንዳመለከተው  በሁለት ጀልባ ተጭነው  በገልፍ-ኦፍ  ኤደን ባህር ወደየመን  በማምራት  ላይ እያሉ  ነው  በተነሳ  ሀይለኛ  ንፋስና  ማዕበል አስጥሞአቸው  የከፊሉ  አስከሬን  በየመን  ሰላጤ  አካባቢ  የተገኘው  ።

ከ ኢትዮጵያ  በየጊዜው  የሀገሪቱን  የፖለቲካና  የ ኢኮኖሚ  ቀውስ  በመሸሽ ወደ  የመን  በባህር  የሚመጡ  በሺዎች  የሚቆጠሩ  ኢትዮጵያውያን  ለተመሳሳይ አደጋ  እንደተዳረጉና  እንደሚዳረጉ   ይኸው  ዘገባ  አመልክቶዋል።

የየመን  የሀገር  ውስጥ  ሚኒስትር  አብዱል-ቃድር  ከታን  ዋቢ  ያደረገው ዘገባው የመን  በየጊዜው  የሚፈልሱትን  ኢትዮጵያዊ  ስደተኞች  ለመግታት  በቅርቡ  ጥብቅ  እርምጃ  እንደምትወስድ  አስታውቀዋል  ብሎዋል ።

የተባበሩት  መንግስታት  ምንጮች  እንደሚየመለክተው  በ የአመቱ  75 000 ኢትዮጵያውያን  ስደተኞች  ገልፍ-ኦፍ  ኤደንን  ይሻገራሉ  ወይም  ለመሻገር ይሞክራሉ ።

No comments:

Post a Comment