Translate

Friday, November 2, 2012

የኦፌዴንና የኦፕኮ ፓርቲ አመራሮች ጥፋተኞች ተባሉ


ኢሳት ዜና:-የኦሮሞ ፌደራሊስት ዲሞክራቲክ ንቅናቄ ( ኦፌዴን)ና የኦሮሞ ህዝብ ኮንግረስ ፓርቲ አመራሮች ጥፋተኞች ተባሉ

በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ፌደራሊስ ዲሞክራቲክ ንቅናቄ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባና የኦሮሞ ህዝበ ኮንግረስ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ኦልባና ሊሌሳ ከሌሎች 9 የኦሮሞ ተወላጆች ጋር በመሆን በተከሰሱበት ወንጀል ጥፋተኛ ተብለዋል።

ፍርድ ቤቱ ለአቶ በቀለና አቶ ኦልባና የቅጣት ማቅለያ ሀሳብ እንዲያቀርቡ ጥያቄ ቢያቀርብላቸውም ሁለቱም እንዲሁም አንድ ስማቸው ያልተወቀ ተከሳሽ ጥፋተኞች ባለመሆናችን የፍርድ ማቅለያ ሀሳብ የለንም በማለት መናገራቸውን የኦፌዴን ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ነገአ ገልጸዋል ።

ኦፌዴን ቀድሞ በአቶ ቡልቻ ደመቅሳ ይመራ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ደግሞ አቶ በቀለ ነገአ በበላይነት ንቅናቄውን እየመሩ ነው። ኢህኮ ደግሞ በዶ/ር መራራ ጉዲና እንደሚመራ ይታወቃል።

No comments:

Post a Comment