ድምፃችን ይሰማ
ማክሰኞ ሐምሌ 30/2005
‹‹ህሊናዬ የማያምንበትን እንድሰራ ተገድጃለሁ›› አቃቤ ህግ ቴድሮስ ባህሩ
የመንግስት ክስ መጨረሻው በውል እንኳ አልታወቀም፤ ቀጠሮውም ም እንደሆነ የሚታወቅ ነገር የለም!
እንደ ታማኝ ምንጫችን ገለፃ ከመጀመሪያዉ የክስ ምስረታ ጊዜ ጀምሮ በተለይ የማእከላዊ ወንጀል ምርመራ ፖሊሶች በሙያቸዉ ጣልቃ እየገቡባቸዉ ብዙ አቃቢያን ህግ ባለሙያዎች ከፍተኛ ምሬት እንዳለባቸው አስታውሶ፤ የአሁኑ የአቶ ቴዎድሮስ ሙያቸዉን ለቀዉ ከሀገር እንዲሰደዱ ያደረጋቸዉ ዋናዉ ምክንያትም እንደሚታወቀዉ ለረጅም ጊዜ በተጠርጣሪ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላቶች ላይ ስልጠና የተሰጣቸው ሰዎች የሀሰት የሰዉ ምስክርነት ጋዜጠኛም ሆነ ቤተሰብ እንዲገባ ባልተፈቀደበት ሁኔታ በዝግ ችሎት ሲሰማ የቆየ ሲሆን ይህም ተጠናቆ የቪዲዮ መረጃ መቅረብ ተጀምሮ ነበር፡፡
ለጥቂት ቀናት የታየዉ ቪዲዮ መረጃ ለረጂም ጊዜ ሲሰማ የነበረዉን የሀሰት የሰዉ ምሰክርነት ሙሉ በሙሉ ከንቱ ስላስቀረባቸዉ በአቃቢያን ህግ፣ በደህንነትና በፖሊስ መካካከል ከፍተኛ ዉጥረት ተፈጥሯል፡፡ ለዚህም ይመስላል የፍርድ ቤት ቀጠሮዉ አለመከበሩ ብቻ ሳይሆን ለመቼ እንኳ እንደሚቀጥል ሳይታወቅ ሂደቱ ሁን ተንጠልጥሎ የቀረዉ፡፡ አቶ ቴድሮስ ካሉበት ሁነው ሙሉ የነበረዉን ሂደትና መረጃዉን ለህዝብና ሚዲያ ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አላሁ አክበር!
No comments:
Post a Comment