የአካባቢው ማኅበረሰብ ራሱን ለመከላከል እያደረገ ባለው የአጸፋ ምላሽ የተቆጣው የሶማሊያ ልዩ ኃይል፣ ቦምቡን በትምህርት ቤቱ ላይ እንደወረወረው ከአካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ አስተያየታቸውን የሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች ድርጊቱን ‹‹የበቀል እርምጃ›› ሲሉ ገልጸውታል፡፡ የእጅ ቦምቡ ወደ ትምህርት ቤቱ ከተወረወረ በኋላ በርካቶችን ያቆሰለ ሲሆን፣ በጽኑ የቆሰሉት ደግሞ አምስት ህጻናት መሆናቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ ሌሎችም የጥቃቱ ሰላባ መሆናቸው ታውቋል፡፡
በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት የሚመራው እና ከህወሓት ትዕዛዝ የሚቀበለው የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል፣ በምስራቅ ሐረርጌ በተለይም ሜኢሶ በተባለው ከተማ ጥቃት ማድረስ ከጀመረ ረዥም ጊዜ ሆኖታል፡፡ ሆኖም በህወሓት የሚመራው መንግስት ጥቃቱን ለማስቆም ፍላጎት እንደሌለው በተደጋጋሚ ጊዜ ተስተውሏል፡፡ በአስተዳደሩ ስር የሚገኙ ነዋሪዎችን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ ያለበት የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርም፣ ነዋሪዎቹን ከሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ ጥቃት ለመከላከል ባለመፈለጉ፣ ግድያን ጨምሮ ከፍተኛ ጥፋት እየደረሰ ይገኛል፡፡ ዛሬ በትምህርት ቤት ላይ የተወረወረውን ቦምብ ተከትሎ አካባቢው ላይ ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል፡፡
No comments:
Post a Comment