(ርዕሰ አንቀጽ)
የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅና አለአግባብ ለመበልጸግ ያሰቡ አውሮጳውያን በአሜሪካ አካባቢ ያሉትን አገሮች በጥጥና በሸንኮራ አገዳ እያለሙ መጠነሰፊ ሃብት ለማጋበስ በሰላም የሚኖሩ አፍሪካውያንን በግፍ እያጋዙ ዓለማችን እስካሁን ዓይታ የማታውቀውን ዓይነት የባርነት ሥርዓት ለበርካታ ዓመታት አካሂደዋል፡፡ ከአፍሪካ ወደ አሜሪካ በግፍ የተጋዙት ወገኖች በመንገዳቸው ያሳለፉት መከራና ከዚያም ለማሽን እንኳን የሚሰጠው ዕረፍትና ጥገና እነርሱ ተነፍገው ለመቶዎች ዓመታት ከምንም ጋር የማይወዳደርና የማይነጻጸር ሰቆቃ አሳልፈዋል፡፡ የዚህ መራራ ግፍ ውጤት አሁንም አብዛኛውን የዓለማችንን ክፍል እየናጠው ነው፡፡



(ዘ-ሐበሻ) የጦር ሃይሎች የሎጂስቲክስ ዋና ሐላፊ የነበሩት ሌ/ጀነራል ገዛኢ አበራ ቤተሰቦቻቸውን ሰብስበው ስዊድን መግባታቸውን አብርሃ ደስታ ከመቀሌ ባስተላለፈው መረጃ አመለከተ። አብርሃም ገዛኢ ከሃገር የወጡት በጡረታ ለተገለሉ በኋላ ነው በማላት ”የህወሓት ሃላፊዎችማ የያዙትን ይዘው ከሀገር እየወጡ ነው። የተቸገሩ ታችኞቹ ካድሬዎች ናቸው። እንደ አለቆቻቸው ወደ ዉጭ በመኮብለል የግል ደህንነታቸው መጠበቅ አይችሉም።” ሲል ትችቱን አስፍሯል።