በልኡል አለም
ዋናዉ ምክንያት የተባለለት ጉዳይ በሰሞኑ የወያኔ መንግስት በኤርትራ ላይ የከፈተዉ ጦርነት ሲሆን መከላከያ ሚኒስቴሩ በጾረና ግንባር ኳ አቲት (Qua’ atit) ወይም አዲ ቀይህ (Adi keyh) አካባቢ ከ20 እስከ 25 ሺ የሚጠጉ የአርበኞች ግንቦት 7 እና የትህዴን ሰራዊት ሰፍሯል የሚል መረጃ ከወታደራዊ ደህነት ክፍሉ ማለትም ባጠቃላይ ከላይ ከተዘረዘሩት ምድቦች በመረጋገጡ መሆኑን ገልጾ ይህን እስከ አፍናጫዉ ድረስ የታጠቀን የአርበኞች ግንቦት 7 እና የትህዴንን ሰራዊት ለማጥቃት ከመከላከያ ሚኒስቴሩ በቀጥታ መመሪያ ወጥቷል፣ መመሪያዉን ተንተርሶ የትግራዩ ነጻ አዉጭ ቡድን መከላከያ አባላትን ለጦርነት ከመሰማራቱ ቀድሞ መረጃዎቹ ባጠቃላይ በኤርትራ ወታደራዊ ደህነቶች እጅ በመዉደቃቸዉ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ያልተገመተና ከፍተኛ አደጋ እንዲገጥመዉ ሆኗል።
በዚህ ምክንያት የወታደራዊ ደህንነቱ ከላይ የተዘረዘሩትን የመረጃ ምድብ ክንፎች ለግምገማ እንዲጠራ የተጠየቀ ሲሆን የሰሜኑ እዝ ደህንነት በበኩሉ የምድብ መረጃዎቹን በግሉ እንደሚገመግም እና ጠቅላይ ሪፖርትም እንደሚልክ አሳስቧል።
የዉስጥ አርበኞችን ተገን ያደረገ ምንጫችን እንደሚገልጸዉ የመረጃ ክፍሉ ምድብ አባላቶች የግምገማ ትእዛዙን በመቃወም የተወሰኑት መሰወራቸዉን አረጋግጧል።
(ወያኔ ማለት… ድመት በመስታወት እራሷን ስታይ ማለት ነዉ)
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
No comments:
Post a Comment