አገቱኒ የምትለውን የግዕዝ ቃል በመጀመሪያ በመዝሙረ ዳዊት ላይ ነው ያየሁዋት ፣ መዝሙር (3)፣ እንዲህ ነበር ሰንጠር ብላ የገባችው ።
ትርጉሙም ….
እግዚያብሔር አንቅቶኛልና እና ነቃሁ
ከአእላፍ ሕዝብ ከከበቡኝም አልፈራም ።
ከአእላፍ ሕዝብ ከከበቡኝም አልፈራም ።
ስለዚህ ( አገቱኒ =ከከበቡኝም ) ማለት ይሆናል ። መያዝም አቻ ቃል ነው ።
ከዚያ ወዲያ ታዋቂው ቦጠሊቀኛ ፣ መምህር ፣ ተመራማሪ ፣ እኔ ደሞ ነብሴ እስኪጠፋ የምወዳቸው ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ለ መጽሃፋቸው አርዕስት አድርገውት ። አዎ አገቱኒ እና መታገት መንፈሳቸውን አንድ ያደረጉልኝ መሳይ መኮንንና ፋሲል የኔ-ዓለም ናቸው ። በመታገት !መስይና ፋሲል ግን ዛሬ መታገታቸውን አብስረዋል ።
ዘርኝነት በተንሰራፋበት ፣ እውነት እንደ ውሃ በተደፋበት ፣ ገዳይ በሚደነፋበት ፣ ተበዳይ አንገቱን በደፋበት ስርዓት ውስጥ ተለማማጭ ስብእና ፣ ተገዢ ልቦና የለኝም ብለው ህውሃትን ሌት ተቀን እየተታገሉት ፣ እየተቃወሙት ፣ እየተፋጩት ያሉ ጥቂቶች አይደሉም ። ያም ሆኑ መስዋትነት ልክ አለውና ፣ የመሳይና የሲሳይ መስዋትነት ፣ ከጥቂቶቹ ከባድ እና ፈታኝ ድፍረቶች እና ቆራጥነቶች ውስጥ አንዱ ነው ። ስለዚህም እነሱን ያገታቸው ፍቅር እኔንም በነካ እጁ ይዳብሰኝ ዘንድ ምኞቴ ነው ። በርቱ ! ከ ጨለማው ልንወጣ ነው ፣ የብርሃኑ ጫፍ ከ ዋሻው ጫፍ ላይ ይታየኛል ። ልናሸንፍ ነው ምክንያቱም ልቤ አልፈራም ፣ አልሸሽም ይለኛል ።
አምላኬ ያቺን ቀን ፣ ያቺን ቀን አምጣት ። ጠላቴን ” ያዝልቅልሽ እስከሚያልቅልሽ !” ብያታለሁና ። ያቺ ቀን ። ትታየኛለች ። እንደ ሰመመን ሳይሆን ፍንትው ብላ !
No comments:
Post a Comment