ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ አዲስ አበባን በማስፋት ስም በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የአዲስ አበባ አጎራባች ወረዳዎችን መሬት ለመቀራመት ሲሰናዳ በተቀሰቀሰበት ከፍተኛ ህዝባዊ አመጽ በመደናገጥ ከመቶ በላይ ንጹሃን ዜጎችን ሲገድል ከአምስት ሺህ በላይ ዜጎችን ደግሞ በየማጎሪያ ካምፖቹ በማሰር ላይ ይገኛል።
Translate
Tuesday, December 29, 2015
ዮናታን ረጋሳ ታሰረ
Saturday, December 26, 2015
የ11ኛው ሰዓት ጥሪ እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ይመለከታል!
Wednesday, December 23, 2015
በነ ኦነግና ግንቦት ሰባት አታሳቡ ይላል ሪፖርተር ጋዜጣ – የሚሊዮኖች ድምጽ

ገዢው ፓርቲ ሕወሃት/ኢሕአዴግ በኦሮሚያና በጎንደር ለተከሰተው ቀዉስ ጣቶቹን በዉጭ ያሉ አመጽ ቀስቃሽ ኃይሎች በሚላቸው ላይ ማድረጉ ይታወሳል። አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ የመንግስት ቃል አቀባይም አፋቸዉን ሞልተው ተቃዉሞ ያሰሙትን በመቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን “ጋኔኖች” ፣ በዉጭ ያሉ “ጋኔኖችን” የሚያንቀሳቀሱ ያሉዋቸዉን ደግሞ “ጠንቁዋዮች” የሚል ከአንድ ትልቅ አገር የመንግስት ቃላቀባይ በጭራሽ የማይጠበቅ ርካሽ ንግግር መናገራቸው ይታወሳል።
Tuesday, December 22, 2015
በሰሜን በጌምድር (ጎንደር) ወልቃይት ፀገዴ፣ ፀለምት በአማራው ላይ ተስፋፊው ተሓህት/ህወሓት የፈጸመው የዘር ማጽዳት ወንጄል (ገብረመድህን አርአያ)
በገብረመድህን አርአያ
ይህ ታሪካዊ መረጃ በተቀነባበረ መልኩ የሚጀምረው ገና ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ (ተሓህት) ሲፈጠር ጀምሮ አስቀድሞ ለማጥፋት ያነጣጠረው በአማራው ህዝብ ላይ እንደሆነ በማስገንዘብ ነው።
ከዚህ በመነሳት የተሓህት ፕሮግራም ገና ከ1967 ጀምሮ የረቀቀው በዲማ ኮንፈረንስ በየካቲት ወር 1968 ከ150 ያነሱ የተሓህት ታጋዮችን በማሰባሰብ ሕጋዊ ሆነ ተብሎ ቢነገርም፣ ሁሉም ታጋዮች ግን አልተቀበሉትም። በመጥፎ መልኩ የተዘጋጀውና አማራውን በማውገዝና ጠላት ብሎ የፈረጀ ነው።
Sunday, December 20, 2015
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባቀረቡት ጥሪ ኢትዮጵያውያን ቅድሚያ ሰጥተው ሊተገበራቸው የሚገቡ ስድስት ተግራት
አርበኞች ግንቦት 7 በሚከተሉት ስድስት ነጥቦች ዙርያ የተቀናጀ ትግል እንዲካሄድ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የትግል ጥሪ ያደርጋል።
Thursday, December 17, 2015
ትግላችንን ተጠናክሮ በአንድነት ይቀጥል! (አርበኞች ግንቦት7)
የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ በያቅጣጫው መነሳቱ የሚያኮራ ነው። ባለፉት 3 ዓመታት ብቻ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ያደረጉትን የመብት ትግል ጨምሮ በደቡብ፣ አማራ፣ አፋር፣ ጋምቤላና በሌሎችም አካባቢዎች በርካታ የነጻነት ትግሎች ተካሂደዋል። አሁን በኦሮምያ እና በአማራ በተለይም በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች እየተካሄዱ ያሉት የነጻነት ትግሎች የአጠቃላዩ የነጻነት ትግል አካሎች ናቸው። በእነዚህ የነጻነት ትግሎች ገዢው ፓርቲ ከህዝብ ጋር ለምንጊዜውም መለያየቱን ለማየት ችለናል።
ከፍተኛ የወያኔ ባለስልጣናት በቋራ ህዝብ ውርደት ተከናንበው ተመለሱ
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ
አባይ ፀሐዬ፣ ደመቀ መኮንን፣ ገዱ አንዳርጋቸውና ሌሎች በዛሬው ዕለት ወደ ቋራ አምርተው ህዝቡን ለመሰብሰብ ሲሞክሩ ህዝቡ በአንድነት አምፆ ከእነሱ ጋር ፈፅሞ መነጋገር እንደማይፈልግ ገልፆ የውርደትና ሀፍረት ጉንጉን አበባ አንገት አንገታቸው ላይ አስሮ መልሷቸዋል፡፡
የጀግናው አፄ ቴዎድሮስ አጥንት ፍላጭ የሆነው ጀግናው የቋራ ህዝብ አሳፍሮ የመለሳቸው እነ አባይ ፀሐዬ በጎንደር ከተማ ሲኒማ አዳራሽ የፀጥታ ኃይሎችን፣ የዞኑን አመራሮች፣ ወሬ ለማዳመጥና እግር ጥሎት የገባውን ህዝብ ለማወያየት ሞክረው ነበር፡፡ ባለስልጣናቱ ፀረ ሰላም ኃይሎችና አሸባሪዎች ያሏቸውን ጠብመንጃ ያነሱ የነፃነት ድርጅቶች ህዝቡ እንዳይደግፍ ሲያሳስቡ ህዝቡ “ቢመጣ ቢመጣ ከእናንተ የባሰ አይመጣ…” ሲል ምላሽ ሰጥቷቸዋል፡፡ በጎንደር ከተማ የሚኖሩ የትግርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች በስማቸው እየነገደ ከሌሎች ቋንቋዎች ተናጋሪዎች ጋር እንዳቆራረጣቸው በመግለፅ ህወሓትን ከሰውታል፡፡ ከዚህ በኋላ የህወሓት ደጋፊም እንዳልሆኑ የአቋም ለውጣቸውን በይፋ አስታውቀዋል፡፡
የጎንደር ከተማ የፀጥታ ኃይሎች ደግሞ በበኩላቸው ከእንግዲህ ወዲህ ወደ ወጡበት ህዝብ አፈሙዝ አዙረው ምላጭ መስበር እንደማይሹና አገዛዙ ወደ ወገናቸው ተኩሱ የሚላቸው ከሆነ አስቀድሞ የጦር መሳሪያቸውን እንዲረከባቸው ጠይቀዋል፡፡
Monday, December 14, 2015
“ኤርትራ የትግራይ ናት”
“ትልቅ ነበርን ትልቅ እንሆናለን” - ህወሃት
ኤርትራ የትግራይ አካል ናት የሚል አስተምህሮና የፖለቲካ ዝግጁነት ቅስቀሳ መጀመሩ ተሰማ። የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ኤርትራ የትግራይ አካል ስለነበረች እንደገና መልሶ በመቀላቀል ታላቋን የአክሱም መንግስት ለመመሥረት የተያዘው አጀንዳ ተግባራዊ ለማድረግ ይቻል ዘንድ አስፈላጊው ሥራ እየተሰራ መሆኑንንም ጠቁመዋል። ለኢትዮጵያ እንደሆነ የሚጠቀሰው “ትልቅ ነበርን ትልቅ እንሆናለን” የሚለው የህወሃት መፈክር ኤርትራን ከትግራይ በመቀላቀል የአክሱምን “ዳግም ልደት” (ህዳሴ) ለመተግበር የታቀደ ነው ተብሏል፡፡
ጨለማው በረታ!! የትግራይ ተገንጣዮች ወስኑ!!
ጠብ መንጃ መፍትሔ አይሆንም!
ወተት ሊገዛ የወጣ ልጅ በድንገት መሃል ግንባሩን በአልሞ ተኳሾች ይመታና ይወድቃል። ግማሹ ይሸሻል። አላስችል ያለው ርዳታ ለመስጠት ይሞክራል። በመካከል እናት የልጇን መውደቅ ትሰማለች። ጨርቋን ጥላ እያለቀሰች አስፋልት መሃል ተዘርሮ የወደቀው ልጇ ላይ ተጠመጠመች። በደም ተጨማልቃ እያነባች ህይወቱን ለመመለስ ፈለገች። ልጅ መሃል ግንባሩን ተወግቶ ነበርና ሕይወቱ አልፋለች። እናት አበደች። “እኔን፣ እኔ ልደፋ … …” አነባች። አስከሬኑን ለመውሰድ ሚኒሊክ ሆስፒታል ተሰለፈች።
Sunday, December 13, 2015
አርበኞች ግንቦት 7 በህወሓት ሰራዊት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱን ገለጸ
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
ጀግናው የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በህወሓት አገዛዝ የጦር ኃይል ላይ ጥቃት በመሰንዘር ከፍተኛ ድልን ተቀዳጀ!!
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ተደጋጋሚ የሽምቅ ውጊያዎችን በማድረግ የህወሓትን መከላከያ ሰራዊት፣ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ ጦር አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የህዝብ አለኝታነቱን እያስመሰከረ ይገኛል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 የመጀመሪያ ምክር ቤት ስብሰባ መግለጫ
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከህዳር 26 ቀን 2008 ዓ.ም እስከ ህዳር 30 ቀን 2008 ዓም ድረስ ሰራዊቱ በሚገኝበት የትግል ቦታ የመጀመሪያውን የምክር ቤት ስብሰባ አድርጎ በስኬት አጠናቋል::
ይህ ስብሰባ የቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርና ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ተዋህደው አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከተሰኘ ወዲህ የተደረገ የመጀመሪያው የምክር ቤት ስብሰባ ነው::
Thursday, December 10, 2015
Wednesday, December 9, 2015
ለወያኔ ድርጊት፣ ምን ስም እናውጣለት (ይገረም ዓለሙ)
ወገንን ጨፍጫፊ ቆዳው የነጣ ነው
በአበሻ የሚጨክን ፈረንጅ ብቻ ነው፤
እያለ የሚያስብ የዋህ ፍጡር ማነው
ጨፈጫፊ ከሆነ አበሻም ጣሊያን ነው
እንቶኔም በተግባር ሲኞር እንቶኔ ነው፤
በአበሻ የሚጨክን ፈረንጅ ብቻ ነው፤
እያለ የሚያስብ የዋህ ፍጡር ማነው
ጨፈጫፊ ከሆነ አበሻም ጣሊያን ነው
እንቶኔም በተግባር ሲኞር እንቶኔ ነው፤
በየግዜው እየከፋ የሄደውን የወያኔ አረመኔነትና የሀገራችንን ጉዞ ወዴትነት ሳስብ ትውስ ያለችኝን ይህችን ስንኝ ወደ ማስታወሻየ ገልብጬ ያኖርኳት በ1980ዎቹ መጨረሻ ግድም ለንባብ ይበቁ ከነበሩት መጽሄቶች ከአንዱ ነው፡፡ ወያኔ ዴሞክራት መስሎ ለመታየት በሞከረበትና ትክክለኛ ማንነቱ ገሀድ ወጥቶ ብዕርን ከጠመንጃ አስበልጦ መፍራት ባልጀመረበት በዛ ወቅት እንዲህ የጻፉት ሰው ዛሬ በህይወት ካሉ ምን ሊሉ እንደሚችሉ መገመት ይቸግራል፡፡
ዐይናችን ተከፍቷል ህሊናችን ነቅቷል (ከአንተነህ መርዕድ)
የመጀመርያው የኬንያ ፕሬዝደንትና የነፃነት ታጋይ ጆሞ ኬንያታ ብዙ ጊዜ የሚጠቀስላቸው፣ ስለ ቅኝ ገዥዎች የተናገሩት እውነት ይህን ይመስል ነበር። “ሚሲዮኖች ወደ አፍሪካ ሲመጡ እነሱ መጽሃፍ ቅዱስ፤ እኛ ደግሞ መሬት ነበረን።
Tuesday, December 8, 2015
ESAT Latest News update Protest Dec 08 2015
የአምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ ግባት መሬት የመጨረሻው መጀመሪያ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በተካሄደባችው አካባቢዎች ሕዝብ የራሱን አስተዳደር እየመደበ ነው!!
ይህንን የሕዝብ ትግል በየትኛውም መልኩ ማገዝ የውዴታ ግዴታ ነው!!
“ትግራይ ወረዳ ውስጥ ያለ የመንግሥት አሰራር በኦሮሚያ ውስጥ … ይገኛል”
“ወደ እውነተኛው ፌደራሊዝም እንመለስ”
* “የአዲስ አበባ መሬት በማለቁ ወደ ኦሮሚያ መሬት እጃቸውን መዘርጋት ጀመሩ”
* “ማስተር ፕላኑ መሰሪ ነው” በቀለ ገርባ
የአዲስ አበባና የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ማስተር ፕላንን በተመለከተ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ያለውን ዝርዝር አቋም በተመለከተ የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባን አዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ በፅ/ቤታቸው ተገኝቶ አነጋግሯቸዋል፡፡
በገዛ አፈ-ሙዙ መቃብሩን የሚቆፍር የሽንፈትን ጽዋ ይጎነጫል! (ሰማያዊ ፓርቲ)
ከሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ
ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ የአዲስ አበባ ከተማንና ዙሪያን ለማከለል ከወጣው የማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ፤ ገቢራዊነትና ሃሳቡን የተቃወሙ የኦሮሞ ተወላጆች እና የዕቅዱ ተቃዋሚዎች፣ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጆች እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንዲሁም የየከተማዎቹ ነዋሪዎች ላይ የኃይል እርምጃ እየተወሰደ እንዳለ የአደባባይ ሀቅ ነው፡፡
ዜጎች እያሰሙት ያለውን ተቃውሞና የሃሳብ ልዩነት በኃይልና በጠብ-መንጃ ለመመለስ የተደረገውም አግባብነትና ኃላፊነት የጎደለው ጭፍን ተግባር እንደሆነ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት በጽኑ ያምናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ፣ መቶ-በመቶ ሁሉንም ተቋማትና መንግሥታዊ መዋቅሮች በጠቅላላ እንደልቡ የሚያዘውና ያሻውን የሚፈጽመው የኢህአዲግ መራሹ ኃይል፣ ልማትንና እድገትን በኃይልና በጉልበት እፈጽማለሁ እንዲሁም አስፈጽማለሁ ብሎ መነሳቱም መሠረታዊ የእብሪት ተግባር መሆኑም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አሳምሮ ያውቀዋል፡፡
Sunday, December 6, 2015
Saturday, December 5, 2015
ልጆች በጥይት አይቀጡም፣ የትኛው መንግስት ዛሬ ተማሪዎችን በጥይት ይደበድባል?
ቢላል አበጋዝ – ዋሽግተን ዲሲ
ዛሬ የዓለም መሪዎች በፓሪ ፈረንሳይ ስለ ዓለማችን ያየር ንብረት ችግሮች እየመከሩ ነው።ችግሩ ደግሞ ቀድሞ ሰለባ ያደረገው ደሃ አገሮችን መሆኑ ግልጽ ነው።ኢትዮጵያም አንድዋ ናት።ከኢትዮጵያ ህዝብ አስራ አምስት ሚሊዮን ለራብ መጋለጡ መደበቅ የማይቻል እውነት ነው።ወያኔ ሃላፊነት ያለው መንግስት ቢሆን እዲህ ጊዜ የማይሰጥ ችግር ላይ ያተኩር ነበር።የአስራ አምስት ሚሊዮን ህዝብ ለራብ መጋለጡን የአውሮፓ ህብረት ጉዳዬ ብሎ ሲመክርበት ህወሃት ይህን ችግር ከፖለቲካ ተቃውሞ መለየት ተስኖት ከውይይቱ እንኳን ለመሳተፍ አልመረጠም።ካአየር ንብረት ችግሩ እጅግ የከፋው የአስተዳደር ጉድለቱ የሚፈጸመው ግፍ ነው በኢትዮጵያችን።ኢትዮጵያ መንግስትዋ ሽብርተኛ ያየር ንብረት ችግሯ በጣም ፈታኝ የሆነበት ዘመን ዛሬ ነው።ያየር ንብረት ችግር ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ልጆችዋን እየገበረች ነው።ልጆች በጥይት ይቀጣሉ።የህወሃት ግፍ ይህ ነው።

ህወሃት የዛሬውን አይበለውና የትግራይ ህዝብን አታግልለታለሁ ሲል “ሃረሽታይ ሸቃላይ” ወይም አርሶአደር ላብአደር ይል ነበር። ለህዝብ እንደቆመ ሁሉ።ዛሬ “መሬት ላራሹ”ን ተረተረት አድርጎ የኢትዮጵያን አርሶ አደር መሬት ንብረቱን ቀምቶ እያራቆተው ይገኛል። ከአርሶ አደሩ አብራክ የወጡትን ልጆቹን ለአርሶ አደሩ በደል ቢነሱ በጥይት ይደበድባቸዋል። የዓለም ዜና ይህን ባያተኩርበትም ዛሬ የኢትዮጵያ ሁኔታ በከፋ መጠን እየተናጋ መሆኑን ማንም ሊክድው አይችልም።በዓለም ተበትነን ያለነው ዜጎች በየሰዓቱ የምንከታተለው ይህንኑ ነው።
ዛሬ የዓለም መሪዎች በፓሪ ፈረንሳይ ስለ ዓለማችን ያየር ንብረት ችግሮች እየመከሩ ነው።ችግሩ ደግሞ ቀድሞ ሰለባ ያደረገው ደሃ አገሮችን መሆኑ ግልጽ ነው።ኢትዮጵያም አንድዋ ናት።ከኢትዮጵያ ህዝብ አስራ አምስት ሚሊዮን ለራብ መጋለጡ መደበቅ የማይቻል እውነት ነው።ወያኔ ሃላፊነት ያለው መንግስት ቢሆን እዲህ ጊዜ የማይሰጥ ችግር ላይ ያተኩር ነበር።የአስራ አምስት ሚሊዮን ህዝብ ለራብ መጋለጡን የአውሮፓ ህብረት ጉዳዬ ብሎ ሲመክርበት ህወሃት ይህን ችግር ከፖለቲካ ተቃውሞ መለየት ተስኖት ከውይይቱ እንኳን ለመሳተፍ አልመረጠም።ካአየር ንብረት ችግሩ እጅግ የከፋው የአስተዳደር ጉድለቱ የሚፈጸመው ግፍ ነው በኢትዮጵያችን።ኢትዮጵያ መንግስትዋ ሽብርተኛ ያየር ንብረት ችግሯ በጣም ፈታኝ የሆነበት ዘመን ዛሬ ነው።ያየር ንብረት ችግር ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ልጆችዋን እየገበረች ነው።ልጆች በጥይት ይቀጣሉ።የህወሃት ግፍ ይህ ነው።
ህወሃት የዛሬውን አይበለውና የትግራይ ህዝብን አታግልለታለሁ ሲል “ሃረሽታይ ሸቃላይ” ወይም አርሶአደር ላብአደር ይል ነበር። ለህዝብ እንደቆመ ሁሉ።ዛሬ “መሬት ላራሹ”ን ተረተረት አድርጎ የኢትዮጵያን አርሶ አደር መሬት ንብረቱን ቀምቶ እያራቆተው ይገኛል። ከአርሶ አደሩ አብራክ የወጡትን ልጆቹን ለአርሶ አደሩ በደል ቢነሱ በጥይት ይደበድባቸዋል። የዓለም ዜና ይህን ባያተኩርበትም ዛሬ የኢትዮጵያ ሁኔታ በከፋ መጠን እየተናጋ መሆኑን ማንም ሊክድው አይችልም።በዓለም ተበትነን ያለነው ዜጎች በየሰዓቱ የምንከታተለው ይህንኑ ነው።
Thursday, December 3, 2015
አርበኞች ግንቦት 7 – የወገኖቻችን ስቃይ፣ ችግርና ብሶት በያለንበት ይሰማን፤ ለመፍትሔውም በጋራ እንነሳ!
አርበኞች ግንቦት 7 – የወገኖቻችን ስቃይ፣ ችግርና ብሶት በያለንበት ይሰማን፤ ለመፍትሔውም በጋራ እንነሳ!
በዚሁ ወቅት በጎንደር ሌላ አሳዛኝ ጉዳይ ተከስቷል። ህወሓት ከሶስት ሺህ በላይ ዜጎቻችንን ያጎረበት እስር ቤት በእሳት ሲጋይ ዜጎች ተቆልፎባቸው እንዲነዱ ተደርጓል። ከእሳቱ በእድል ያመለጡት በጥይት ታድነዋል። ኢትዮጵያዊያን እንዲህ ዓይነቱን ጭካኔ የሚያውቁት በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ጊዜ ነው። ይህን ጥቃት በመቃወም ላይ ያሉ የአማራ ተወላጅ ወገኖቻችን ትግል ፍትሀዊ በመሆኑ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ከጎናቸው ይቆማል።
Wednesday, December 2, 2015
አንድ:- ከመጠምጠም መማር ይቅደም
(ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)
በፌስቡክ የምንሰባሰበው ለመወያየት፣ አንዱ ከሌላው እንዲማር፣ መረጃዎችን በነጻነት እንድንለዋወጥ፣ ይህንን ሁሉ በማድረግ ራሳችንን ለማሻሻል፣ የእኛ መሻሻል እየተራባና እየተባዛ የአገርና የሕዝብ መሻሻል እንዲሆን፣ ከተቻለንም ከአገራችንና ከሕዝባችን አልፈን የምንታይ የዓለም አካል እንድንሆን መስሎኝ ነበር፡፡ ሳየው በዚያ መንገድ ላይ ያለንና ፌስቡክን ለበጎ ዓላማ እየተጠቀምንበት ያለን አይመስለኝም፤ ስለዚህ ወይ መታረም፣ አለዚያም በፌስቡክ ጊዜ ማጥፋቱን መተው ምርጫ ሊሆንብን ነው፡፡
Tuesday, December 1, 2015
Subscribe to:
Posts (Atom)