Translate

Monday, May 4, 2015

የየመን ጦርነት፤ የኢትዮጵያዉያን ፍዳ

በስደተኛ አቅሟ ያጠራቀመችዉን ጥሪት ለቦምብ ሚሳዬል አረር ገብራ ከአደን ዳግም ለተሰደደችዉ ኢትዮጵያዊት ጦርነቱ ከፋ፤ «የሚጠጣ ዉሐ ጠፋ፤ ወይም ተመረዘ»-ከሚለዉ ወሬ ያለፈ የጦርነቱ ሰበብ ምክንያት፤ የመርዙ ደረጃ፤ የመርዙ ምንነት፤ የመራዡ ማንነትም ግልፅ አይደለም።

ኢትዮጵያዉን ስደተኞች ደቡብ አፍሪቃ ላይ እሳት ተለቀቀባቸዉ።ነደዱ-ሞቱ።ሜድትራኒያን ባሕር ዉስጥ ሰምጠዉ አለቁ።ሊቢያ ላይ ታረዱ።እስራኤል ዉስጥ ዜጋም ሆነዉ ይዋረዱ-ይገለሉ-አሁን ደግሞ ይደበደባሉ።የመን ዉስጥ በባዘነ-ጥይት-ሚሳዬል ተገደሉ።

ከወራት በፊት ወይንሸት ሞላ ከ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ በዋስ ስትፈታ ስለ አያያዟ እና ስለ ነበረው ሁናቴ ከነገረ-ኢትዮጵያ ጋዜጣ ጋር ቃለመጠይቅ አድርጋ ነበር.

Woyinshet Molla
. ብዙ ነገር ደርሶባታል... ወኔዋ ግን አሁንም አልተፈታም! ቃለመጠይቁ ይሄን ይመስል
ነገረ ኢትዮጵያ፡- አንዋር መስጊድ አካባቢ ተይዘሽ ከታሰርሽ በኋላ ለምን መስጊድ ሄደች የሚሉ አካላት ነበሩ፡፡ ለመሆኑ እንዴትና ለምን ነበር የሄድሽው?
ወይንሸት፡- የሄድኩበት ምክንያት ግልጽ ነው፡፡ በእርግጥ እኔ የሄድኩበትን ብቻ ሳይሆን በተለይ በገዥው ፓርቲ በኩል የሙስሊሙን ማህበረሰብ እንቅስቃሴም ባልሆነ መንገድ ትርጉም እየተሰጠው ነው የሚገኘው፡፡ የሙስሊሙን እንቅስቃሴ እስላማዊ መንግስት ለመመስረት የሚደረግ እንደሆነ አድርገው በተሳሳተ መንገድ ያቀርቡታል፡፡ የእኔንም ከዚህ በተለየ ሁኔታ አይደለም ያቀረቡት፡፡ ምን አልባት የእኔ ይለያል ከተባለ ፖለቲከኛ በመሆኔ ሊሆን ይችል ይሆናል፡፡ ሆኖም እኔም የሄድኩት እንቅስቃሴውን ለማየት ነው፡፡ ይህን ለማየት የሄድኩበት ምክንያት አንደኛ ገዥው ፓርቲ ሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ሰላማዊ አይደለም ብሎ ስለሚፈርጅ ነው፡፡ ሙስሊሞች ደግሞ እንቅስቃሴው ሰላማዊ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ለህዝብ እንደቆመ እንደ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አባልነቴም ሆነ መሪ ለመሆን እንደምትፈልግ አንዲት ሴት ቦታው ላይ ተገኝቼ ነገሮችን ማረጋገጥ ስለነበረብኝ ቦታው ላይ ተገኝቻለሁ፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ፡- የተያዝሽበት ሁኔታስ ምን ይመስላል?

Sunday, May 3, 2015

ሰበር ዜና፣ በሊቢያ የተሰውት ኢትዮጵያውያን ክርስትያኖች “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” በመባል እንዲጠሩና ገድላቸውም በየዓመቱ እንዲዘከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ!!!

ሰበር ዜና፣ በሊቢያ የተሰውት ኢትዮጵያውያን ክርስትያኖች “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” በመባል እንዲጠሩና ገድላቸውም በየዓመቱ እንዲዘከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ!!!
Semaetate Ethiopia Bemdere Libya

የባለስልጣናቱ ድንቁርና እና የልማታዊ ሀዘንተኞች አክራሞት!

አዜብ ጌታቸው
ከሁሉ አስቀድሜ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በሃገራችን በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በወረደው የመከራ ናዳ ግንባር ቀደም ተጠቂ የሆኑትን ሰማዕት ወገኖቻችንን ነፍስ ጌታ በቀኙ ያስቀምጣት ዘንድ በጸሎት የታገዘ ምኞቴን ልገልጽ እወዳለሁ። በማስከተልም ድንገተኛና አስደንጋጩ ሃዘን ለጎዳው የቅርብ ቤተሰባቸውና በአጠቃላይም ለመላው ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁሉ መጽናናትን አብዝቶ ይስጠን እላለሁ።
ውድ ወገኖቼ! ያለፉት ሳምንታት እንደ ሃገር፦ ለኢትዮጵያ እንደ ዜጋ፦ ለኢትዮጵያዊው ሁሉ አሳዛኛ፤ አስደንጋጭ፤ አሰቃቂ፤ አስቆጭ …. ነበሩ። ሃዘኑ የሚከብደው ደግሞ ለደረሰብን ጥቃት ምንም ምላሽ መስጠት የማንችል መሆናችንን ስናስብ ነው። በጀግንነት ያለፉት ሰማዕታት ያልሞቱት እኛ በቁም ያለነው ብቻ የሞትነው ሞት ይህ ነው። ጥቃት መመከት አለመቻላችን!። ለማንኛውም ሁላችንም በዚሁ ስሜት የከረምን በመሆኑ መጽናናትን ይስጠን ብዬ ልለፈው፡፡
የዛሬው ጽሁፌ የሚያጠነጥነው በነኝሁ በመከራ ሳምንታት ውስጥ በታዘብኳቸው ሁነቶች ዙሪያ ነው። በተለይም የህውሃት መንግስት ባለስልጣናትና የደጋፊዎቻቸውን ልማታዊ የሃዘንተኝነት አክራሞት ይመለከታል።

Friday, May 1, 2015

አውነቱ ይውጣ! – መስፍን ወልደ ማርያም


11210496_815275908557345_6919471305989819924_n
ሴቶችን በወንዶች ፊት፣ ወንዶችን በሴቶች ፊት ልብስ እያስወለቁ የአካላቸውን ክፍሎች ሁሉ ለማየት የሚያስችል አንቅስቃሴ አንዲሠሩ ማስገደድ በሽተኞችን ያስደስታል፤ የምርመራ ዘዴ ግን አይደለም፤ ውርደት እንዲሰማቸው ከሆነ በወራዶች ሰዎች ፊት የምን መዋረድ አለ? ወራዶች እነሱ ደረጃ ላይ ከእነሱ ጋር ያስተካክላሉ አንጂ አያዋርዱም፤ በሌላ አነጋገር ወራዶች አያዋርዱም፤ ወራዶቹ ደንቆሮዎችም ሆነው ነው እንጂ ልብስ የሚያስወልቁ እነሱ ብቻ አይደሉም፤ ሀኪሞችም ልብስ አስወልቀው፣ አጋድመው በጣታቸውም ሆነ በመሣሪያ የፈለጉትን የአካል ክፍል አንደፈለጉ ያደርጉታል፤ ወራዶቹና ደንቆሮዎቹ ከሚያደርጉት የሀኪሞቹ የሚለየው ሀኪሞቹ ሰዎችን ለማዳን ሲሉ ነው፤ ወራዶቹና ደንቆሮዎቹ ግን የራሳቸውን ሱስ ለማርካት፣ የራሳቸውን ህመም ለማስታገስ ነው፤ ወራዶቹንና ደንቆሮዎቹን ከመለዮአቸው አራቁቻቸዋለሁ!

Detail of Rights Violation on Zone9 Bloggers and Journalists

Ethiopia Human Rights Project

It is now solid one year since the arrest of Zone9 blogger and journalists. there had been 27 court hearings, 86 days of interrogation at the notorious “Meakelawi” interrogation center before they moved to their current detention place in “Kality” and “Kilinto”. during their stay they faced many rights violation. this rights violation had also been reported for the united nations working group for arbitrary detention.
On the commemoration of their arrest the summary of the rights violation was made public for readers and followers of the case of for the last one year. attached is the summary of the rights violation.
Violation on Zone9 Bloggers

አሜሪካ አይሲስን ለምን ፈጠረችው?

(ክንፉ አሰፋ)

usisis

ግብጽ የሃያ አንድ ክርስቲያን ዜጎችዋን በአይሲስ መታረድ ዜና እንደሰማች ዝም ብላ አልተቀመጠችም ነበር። ብሄራዊ የሃዘን ቀንም አላወጀችም። እንዲህ ነበር የሆነው። ከመቅጽበት ተዋጊ አውሮፕላኖችዋን አስነስታ ወደ ሊቢያ ላከቻቸው። የአይሲስ አራጆች የተከማቹበትን ደርና የተሰኘ ስፍራ እያከታተለች በቦምብ ቀጠቀጠችው። ብዙ አራጆች በድብደባው አለቁ። እንደ ግብጽ አጀማመር ቢሆን የሊብያው አይሲስ ክንፍ ድሮ-ድሮ ከምድረ-ገጽ ይጠፋ ነበር። ግና አልሆነም። አሜሪካ ጣልቃ ገባች። ግብጽ የአሜሪካን “ጸረ-ሽብር” ዘመቻ በማገዝዋ ምስጋና ማግኘት ሲገባት በተቃራኒው ተወገዘች። ከጥቂት ድብደባ በኋላ ፔንታጎን ግብጽን አስጠነቀቀ[0]። የኦባማ አተዳደርም ደብደባው በአፋጣኝ እንዲቆም ቀጭን መልእክት ላከ። ይህ ድርጊት ከዚህ ቀደም ስለ አይሲስ አፈጣጠር ኤድዋርድ ስኖደን[1] የለቀቀው ምስጢራዊ መረጃ ጋር ተዳምሮ በአሜሪካ ላይ የነበረውን ጥርጣሬው አጠናከረው።