Translate

Tuesday, February 28, 2017

ታጋይ ጎቤ መልኬ በአዴት ጦርነት ተሰዋ፤ “የህወሃት ወራሪ ሃይል ጉዳት ደርሶበታል”


  • “ጎቤ ሲሰዋ አዳዲስ ጎቤዎች ትግሉን ተቀላቅለዋል’’
“አርበኛ ጎቤ መልኬ ተሰዋ” ሲሉ በአካባቢው የሚገኙ የጎልጉል መረጃ አቀባዮች ገለጹ። ህወሃት የሚመራው ሰራዊት ክፉኛ ጉዳት ደርሶበታል። ዜናው ኢህአዴግ በሚያስተዳድራቸውም ሆነ በሚደጉማቸው መገናኛዎች ይፋ አልሆነም። ለነጻነት ሃይሎች ጋር ግንኙነት አላቸው የሚባሉ አካላትም ይህ ዜና እስከታተመበት ድረስ በግልጽ ያሉት ነገር የለም። አርበኛ ጎቤ እራሱን እንዳጠፋም የሚገልጹ አሉ።

Tuesday, February 21, 2017

የጦር መሳሪያ ዋጋ አሻቀበ፤ ክላሽንኮቭ እስከ 60 ሺህ ብር ይሸጣል፣ መሳሪያ ቁልፍ ሃብት ሆኗል!

  • ሱዳንና ህወሃት የመሳሪያ ዝውውርን ለመግታት ተስማሙ
  • ትግራይ ክልል ኢትዮጵያን ወክሎ ከሱዳን ጋር ስምምነት አደረገ
ከወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ የተቀሰቀሰዉ አመጽ ማህበራዊ መሰረቱን እያሰፋ በጎንደርና በጎጃም የተለያዩ ዞኖችን፣ ወረዳዎችን፣ የከተማ አስተዳደሮችና የገጠር ከተሞችን ያዳረሰ ህዝባዊ እምቢተኝነት ለመሆን በቅቷል። ይኸው ህዝባዊ እምቢተኝነት በጦር መሳሪያ የታጀበ መሆኑ ደግሞ ከሌሎች የተለየ አድርጎታል። በተለያዩ ማህበራዊ ገጾች፣ የሚዲያ ውጤቶች እንዲሁም “የአማራ ተጋድሎ” በሚል ስያሜ የሚታወቁት ክፍሎች ባቋቋሟቸው መገናኛ መንገዶች በተደጋጋሚ እንደሚገለጸው የሚወድቁ ብቻ ሳይሆን የሚጥሉ የተጋድሎ ሃይሎች እየተበራከቱ ነው። አንዳንዴም የድል ብስራት ያውጃሉ። ትንቅንቁም ቀጥሏል።

ምዝበራ በየፈርጁ (ተሻለ መንግሥቱ)

ተሻለ መንግሥቱ 
ይህ የፍዳና የሰቆቃ ዘመን እስኪያልፍና የማይቀረው ወርቃማ የነፃነት ዘመን እስኪመጣ በሰመመን የምቆይበትን ብልኃት ባገኝ ወደድኩ፡፡ እንዲያ ዓይነት ጥበብ ተገኝቶ እንደእሥራኤሉ ፕሬዝደንት (ኤርየል ሻሮል) በሞትና በሕይወት መካከል አሸልቦ ሳይሰሙ ሳይለሙ ብዙ ጊዜ መቆየት ለእንደኔ ያለው ሰው ተፈልጎ አይገኝም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የምንኖር ጥቂት የማንባል ዜጎች አብዛኛው የምንሰማውና የምናየው ነገር ግራ እያጋባን በዚህ ሁኔታ ውስጥ ከመኖር ይልቅ አለመኖርን እንመርጣለን፡፡ አስደንጋጭ ወቅታዊ ሁኔታ ውስጥ ተዘፍቀናል፡፡ ራሳችንን እየታመምን የምንኖር አለን – በበኩሌ በጣም እያመመኝ እንደምኖር ብደብቅ ዋሸሁ፡፡
Kinfe Dagnew (B. Gen.), the chief executive officer (CEO) of the Metal & Engineering Corporation (MetEC)
Kinfe Dagnew (B. Gen.), the chief executive officer (CEO) of the Metal & Engineering Corporation (MetEC)
ዛሬ ጧት ነው፡፡ ከአንድ ወዳጄ ጋር እንጫወታለን – ስለወያኔዎች ሁለንተናዊ የምዝበራ ሥልትና የሙስናው ቅጥአልባነት ነበር በንዴት እየተንጨረጨርን የምናወጋው፡፡ የቀራቸው እኮ የለም፤ ሁሉንም እነሱ ተቆጣጥረውታል፡፡ በአንዲት ቀን አዳር መክበር የሚቻለው ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ መሆኑን ባለፉት 25 ዓመታት ውስጥ በተደጋጋሚ አስመስክረዋል፡፡ በአንዲት ቀን አዳር መክበር ብቻም ሳይሆን በአንዲት ቀን አዳር ማደኽየትም ሆነ አላንዳች በቂ ምክንያትና ፍትሃዊ ፍርድ አንድን ዜጋ መቅ ማውረድም እንደሚችሉ አስተዋይ ልቦና ላለው የዓለማችን ዜጋ አሳይተዋል፡፡ ላኪዎቻቸው ግን በወያኔዎች ዕኩይ ድርጊት ቢደሰቱ እንጂ አይገረሙም፡፡ እነዚህ የስቃያችን አበጋዞች ውጤቱን አስቀድመው የማያውቁትና ሲቻላቸው ደግሞ በርቀትም በቅርበትም የማይቆጣጠሩት አንድም ድርጊት በዓለም እንደሌለ የሚገነዘቡ  የፕላኔታችን ገዢዎች ናቸው፡፡

Sunday, February 19, 2017

በኢትዮጵያዊነትና በኢትዮጵያ ሀገራዊ ኣንድነት ላይ የተቃጣው ጦርነትና የአርበኞች ግንቦት 7 ሀገር ኣድን ትግል (ነዓምን ዘለቀ)

ነዓምን ዘለቀ
ራሱን ህዝባዊ ወይኔ ሃርነት ትግራይ  በማለት  በሚጠራው የጸረ-ኢትዮጵያ መሰሪዎች አምባገነናዊ አገዛዝ ላለፉት ሃያ አምስት አመታት  የዘለቀ  ስቃይ እና ጥቃት ኢላማዎች የነበሩት የኢትዮጵያ አንድነትና ኢትዮያዊነት ብቻ ሳይሆኑ  የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችም በተናጠል እና በየተራ ግፍ እና ስቃይ ሲቀበሉ ቆይተዋል ፣ አሁንም በከፋ መልኩ ስቃዩ ቀጥሏል። ጸረ ኢትዮጵያዊው ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ በተደራጀ መልኩ  የጥፋት ሰይፉን በዋናነት የመዘዘበት  ኢትዮጵያዊነት ደግሞ አንዳንዶች እንደሚያምኑት የብሄር ብሄረስቦች ማለትም የኦሮሞው፣የአማራው ፣ የትግሬው፣የሶማሌው ፣የሲዳማው፣የጉራጌው ፣ የአፋሩ፣የከምባታው  እንዲሁም የሌሎች ብሄረሰቦች  ድምር ማንነት ብቻ ሳይሆን  ኢትዮጵያዊነት ከብሄሮች ድምር (The sum of its parts) በላይ ነው።  ኢትዮጵያዊነት ለዘመናት የተገነባ ማንነት ነው። የየትኛውም ብሄር ወይም ነገድ ባህልና ቋንቋ ብቻውን ኢትዮጵያዊነትን አይገልጸውም፣ አይበቃውም፣  አይተረጉመውም።
Neamin Zeleke a member of Patriotic Ginbot 7
ነዓምን ዘለቀ
ኢትዮጵያዊነት ሚሊዮኖች በጋራ የምንጋራው ውስጣዊ ማነትታችን ነው። ስነ-ልቦናዊም ህሊናዊ ባህሪያት ያሉት  ልንገልጸው ከምንችለው በላይ ረቂቅ ነው ፡፡ ለዘመናት የተገነባውና ሚሊዮንኖች በጋራ የሚጋሩት ይህ ማነንታችን መሰረታችን ከሆነው ብሄር ማንነት በላይ ሁለመናችንን የሚገዛን  መንፈስ  ነው።ድሃ ብንሆንም፣ በጨቋኝ ስርዓቶች ወስጥ ብናልፍም  የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎችን አሳፍሮ  በደም የተከበረው፣በማህበራዊ ትስስር የተገመደው ኢትዮጵያዊ ማንነታችን ያረካናል፣ ያጠግበናል። ከሁለት ብሄር  እና ከዚያ በላይ ቤተሰብ የተገኙ ሚሊዮኖች  ኢትዮጵያዊነትን በብሄር አጥር እንደማናቆመው  ህያው ማሳያዎች ናቸው። በአዲስ አበባ፡ በአዳማ ፣በደሴ፡ በሃረር፣ በድሬዳዋ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፡ ጅማ፣ አዋሳ  በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ዋና ዋና ከተሞች  ተወልደው ያደጉ ሚሊዮን ከተሜዎች  (Cosmopolitans) በመሆናቸው ራሳቸውን ከተወለዱበት ብሄር/ዘውግ ማነንት ጋር የሚያቆራኙበት ሁኔታ ባለመኖሩም፣ ማንነታቸው ኢትዮጵያዊነት ነው።