Translate

Friday, April 29, 2016

የወያኔ መንግስት አቶ ኦኬሎ አኳይ፣ ለማሳፈን ለደቡብ ሱዳን መንግስት 39.5 ሚሊዮን ዶላር መክፈሉ ተነገረ


የቀድሞ የጋምቤላ ፕሬዚደንት አቶ ኦኬሎ አኳይ የጋምቤላ ጭፍጨፋን በተመለከተ ለፍርድ ቤት ማብራሪያ ሰጡ። የጭፍጨፋውን ሂደት በማዛባት፣ የተሳሳተ መረጃ ለህዝብ እንዲያቀርቡ በመገደዳቸውና ጭፍጨፋው የህሊና ሰላም ሰለነሳቸው ፕሬዚደንትነታቸውን ጥለው ድንበር አቋርጠው መሸሻቸውን በጽሁፍ ለፍርድ ቤቱ አስታውቀዋል።

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ አዲሱ ትውልድ የኢትዮጵያን አንድነት እንዲጠብቅና የታሪክ ህፀፆችን እንዲያርም ጥሪ አቀረበ

የኢትዮጵያ አንድነት የመጠበቅና የታሪክ ህፀፆችን ማረም ከአዲሱ ዘመንት ዲሞራቶች ይጠበቃል ሲል ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ገለጸ። ታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ “ የዘንድሮ ግንቦት 20” በሚል ርዕስ ሰሞኑን ከወህኒ ቤት ለመገናኛ ብዙሃን በላከው ፅሁፍ ኢህአዴግ ወደስልጣን የመጣበትን 25ኛ አመት በማስመልከት ያለፉትን 50 አመታት የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ሁኔታ በመገምገም ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እንደሚያስፈልግ አስገንዝቧል።
በኢትዮጵያ ተማሪዎች ትግል ውስጥ የነበረው የሃይል አሰላለፍ እንዲሁም በህብረ-ብሄርና በብሄር ፓርቲዎች መካክል የነበረውን ልዩነት በመዘርዘር ለኢትዮጵያ ችግር ዘላቂ መፍትሄ እንዲበጅ ጥሪ አቅርቧል።
“ተማሪዎች እንቅስቃሴያቸውን ከጀመሩ ከ55 ዓመታት በኋላም የዮሃንስና የምኒሊክ የ19ኛው ክፍለ ዘመን ፖለቲካ የፈጠረው ሽኩቻ የኢህአዴግ ቅኝት ጸረ-ዲሞክራሲ እንዲሆን ምክንያት ከሆኑት ግብዓቶች መካከል አንዱ ሆኖ ይገኛል ያለው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሲያጠቃልልም “የታሪክ ጣጣ የኦሮሞና የሶማሌ ብሄርተኞችን ነፍስ ዕረፍት እየነሳ ነው፥ የታሪክ ህፀጾች የማይቀበሉ ቀላል የማይባሉ የፖለቲካ ሃይሎችም አሉ፥ ይህ ሁሉ ተደማምሮ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የተጋረጠ አደጋ ነው፣ መፍትሄውም ከአዲሱ ዘመን ዲሞክራቶች ይጠበቃል” በማለት ለሃገሪቱ ችግር ዕውነተኛና ዘላቂ መፍትሄ እንደሚጠበቅ ጥሪ አቅርቧል።
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ከመስከረም ወር 2004 ጀምሮ በአሸባሪነት ተከሶ በወህኒ ቤት የሚገኝ ሲሆን፣ የ18 ዓመታት እስር እንደተፈረደበት ይታወቃል። ክሱም ሆነ ፍርዱ እውነትም ሆነ ህጋዊ መሰረት እንደሌለው ለማመልከት ወይንም በፖለቲካ አመለካከቱ መታሰሩን ለማስረዳት በጽሁፉ ግርጌ “የህሊና እስረኞች” ሲል አስፍሯል።
 

Thursday, April 28, 2016

በጋምቤላው ጭፈጨፋ የደ/ሱዳን ሹመኞች እጅ መኖሩን አንድ የአገሪቱ የጦር ጄ/ል አጋለጡ

“ ባለሰልጣኑ በጋምቤላው ጭፍጨፋ ዙሪያ አካፋን አካፋ ብለው መጥራት ይገባቸዋል” ሌ/ጄኔራል ዲቪድ ያ ኡ ያ ኡ
ኢትዮጵያ ዛሬም ለባእዳኖቹ ምቹ አልጋ ፣ለልጆቿ ግን ቀጋ የመሆኑዋ ጉዳይ እያነጋገረ ነው
ከሳምንት በፊት በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላ ክልላዊ መስተዳደር በሚገኙ የኑኢር ማህበረሰብ ላይ ከጎረቤት ደ/ሱዳን አንደመጡ የሚነገረላቸው እጅግ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ እና የደ/ሱዳን የመከላከያ ሰራዊቱን የድምብ ልብስ ያጠለቁ መሆናቸው የተነገረላቸው የሞራሌ ጎሳ ተወላጆች በ 10 የኑዊር መንደሮች ላይ በከፈቱት የጅምላ የተኩስ እሩምታ ከ 200 በላይ ሰዎች ህይወትን በመቅጠፍ ከ100 በላይ ጨቅላ ህጻናትን ደግሞ አፍነው በመወሰድ ፣ከ 2ሺህ በላይ የቀንድ ከበቶቻቸውን በመዝረፋቸው ሳቢያ በበርካታ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊናኦች ዘንድ ከፍተኛ የሆነ ብሄራዊ ሃዘን እና ቁጭት መቀሰቀሱ አይዘነጋም።

ሰበር መረጃ…. ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የነጻነት ሀይሎችን ተቀላቀሉ!

የትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን የመከላከያ ሚኒስቴር አመራሮች የደረሳቸዉን መረጃ ተገን በማድረግ 11.250 ( አስራ አንድ ሺ ሁለት መቶ ሐምሳ ) የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በ5 ወራት ጊዜ ዉስጥ ከየመን ከሱዳናና ከሊቢያ ወደ ኤርትራ በመጓዝ አርበኞች ግንቦት 7ን ተቀላቅለዋል!!
ይላል… በሶስቱም ሐገራት የኢትዮጵያ ኢንባሲዎች ላይ የተሰመየዉ የመረጃ ቃል አቀባይ።
ምንጫችን እንደጠቀሱት የወያኔ ባለስልጣናት ከፍተኛ ድንጋጤ ላይ ወድቀዋል! 
በተለይም የመንና ሊቢያ የሚገኙ ብዛት ያላቸዉ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰን በግፈኛዉ አጋዚ ከምንገደልና የወያኔ የግፍ እስር ቤቶች ዉስጥ ከምንማቅቅ ብሎም ማእበል ከሚበላን በረሐ ሄደን መስዋትነት በመክፈል ሐገራችን ነጻ ብናወጣ እንመርጣለን በሚል ዉሳኔ! ከሊቢያዋ ቶብሩክ ( TOBRUK ) እና አካባቢዉ በመነሳት የሐኒሽ ደሴቶችን በጀልባ በማቋረጥና የሱዳንን ድንበር በመጣስ ወደ አርበኞቹ ተቀላቅለዋል ።
ወታደራዊ ደህንነቱ ከፈተኛ ስጋት ላይ ከመዉደቁ የተነሳ ለሐገር መከላከያ ያቀረበዉን መረጃዎች ተንተርሶ የመንና ሊቢያ የሚገኙ ስደተኞችን ወደ ሐገር ቤት የመመለሱ ስራ ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ተወስኖ ወያኔያዊያን ባለስልጣን ያስመረሩትን ወጣት ትዉልድ ለማታታለልና ወደ ሐገር ለመመለስ የትራንስፖርት ወጪዎችንና የጉዞ ሰነድ ዝግጅቶችን በመበጅት ስራ ላይ ተጠምደዋ።
ይህን በተመለከተ ከአርበኞች ግንቦት 7 ወይም ከሌሎች የነጻነት ሐይሎች የተገኘ ፍንጭ ባይኖርም ከትግራዩ ነጻ አዉጪ ቡድን በኩል ግን እዉነታዉን የሚያረጋግጡ ድርጊቶች እየተስተዋሉ ይገኛሉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )
 

Thursday, April 21, 2016

በጋምቤላ የተጨፈጨፉት ዜጎች ጉዳይ ኢትዮጵያውያንን ማነጋገሩን ቀጥሎአል


ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓም በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች የተገደሉት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ የአለምን ትኩረት በሳበት በዚህ ወቅት፣ የደቡብ ሱዳን መንግስት ምንም አይነት መግለጫ አለማውጣቱ ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለጥቃቱ አፋጣኝ መልስ አለመስጠቱ እንዲሁም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከባድ የሆነውን አገራዊ ጉዳይ ትተው ወሳኝ ላልሆነ ስብሰባ ስዊድን መገኘታቸው ኢትዮጵያውያንን እያነጋገረ ነው። 

Wednesday, April 20, 2016

አሰቃቂው የጋምቤላ ጭፍጨፋና የፀጥታ ኃይሎች አሠላለፍ

• ራሱን ‹‹የደቡብ ሱዳን ቡድን›› በማለት የሚጠራው የሙርሌ ጎሳ ታጣቂ ቡድን የደቡብ ሱዳንን ወታደራዊ ዩኒፎርም በመልበስና ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎች በመታጠቅ መቼ እንደተነሳ እስካሁን ማረጋገጫ ባይገኝም፣ ዓርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓ.ም. ለቅዳሜ አጥቢያ ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጋምቤላ ደረሰ፡፡
• ታጣቂው ኃይል ከደቡብ ሱዳን ግሬት ስቦር ግዛት ተነስቶ፣ በሁለት መንገዶች (ጆር እና ኦኛላ) 175 ኪሎ ሜትር አቋርጦ በኑዌርና በአኙዋ ዞኖች በሚገኙ ሦስት ወረዳዎች ተሰማራ፡፡
• ‹‹የደቡብ ሱዳን ቡድን›› እያለ ራሱን የሚጠራው የሙርሌ ጎሳ ታጣቂ ኃይል በወታደራዊ ሬዲዮ መረጃ እየተለዋወጠ በተመሳሳይ ሰዓት በከፈተው ተኩስ፣ ምናልባትም በታሪክ ዘግናኝ የሚባል ግድያ በሰው ልጆች ላይ ፈጽሞ ግዳዩን ይዞ በድል ዜማ ታጅቦ ወደመጣበት መመለሱ ተነግሯል፡፡

Tuesday, April 19, 2016

በጋምቤላ የሟቾች ቁጥር 230 መድረሱንና ከ140 በላይ ህጻናትና ሴቶች መወሰዳቸውን የአካባቢው ምንጮች ገለጹ


ሚያዚያ ፲፩(አሥራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው አርብ፣ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓም በጋምቤላ በከፍተኛ ሁኔታ የተጣቁ ወታደሮች በኑዌር ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ በፈጸሙት ጥቃት፣ መንግስት እንኳን ባመነው፣ 208 ሰዎች ሲገደሉ፣ ከ100 በላይ ቆስለዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ህጻናት ተወስደዋል፣ ከ2 ሺ ያላነሱ የቀንድ ከብቶችም ተወስደዋል።የአካባቢው አስተማማኝ ምንጮች እንደሚሉት ዋናው ጥቃት በተፈጸመበት በጅካዎ እና በላሬ መስመር ብቻ እስከዛሬ ቀን ድረስ የ230 ሰዎች አስከሬን ተገኝቶአል። ተጠልፈው የተወሰዱት ህጻናት ቁጥር ደግሞ 143 ደርሶአል። በማኩዌ አካባቢ በተፈጸመው ጥቃት ምን ያክል ሰዎች እንደሞቱ ገና እየተጠራ በመሆኑ፣ የማቾች ቁጥር ከተጠቀሰው በላይ ይሆናል ሲሉ እነዚሁ ምንጮች ተናግረዋል። ጥቃቱ በተፈጸመበት አካባቢ ሰፍረው የሚገኙ ዜጎችን መንግስት ወደ ጋምቤላ ከተማ እየወሰዳቸው መሆኑንም ምንጮች አክለዋል። በመከለከያ ቦታ የፌደራል ፖሊስ አባላት በአንዳንድ አካባቢዎች ዛሬ ቅኝት ሲያደርጉ ታይተዋል።

በጋሚቤላ ወገኖቻችን ላይ ለደረሰው ጭፍጨፋ ተጠያቂው ወያኔ ነው!!!

ባለፈው ዓርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ድንበር ጥሰው በመግባት በላሬና ጃካዋ ወረዳዎች በሚኖሩ የኑዌር ወገኖቻችን ላይ ጭፍጨፋ ማካሄዳቸውን በአገዛዙ ቁጥጥር ሥር ያሉ ሚዲያዎች ጭምር ዘግበዋል። 
ህወሃት ሥልጣን ከተቆጣጠረ ወዲህ በጋምቤላ ክልል ነዋሪ በሆኑ ወገኖቻችን ላይ እንዲህ አይነት የጅምላ ጭፍጨፋ ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው አይደለም። በ1996 የህወሃት ልዩ ጦር የተሳተፈበት የዘር ማጥፋት ወንጀል በአኝዋክ ተወላጆች ላይ ተካሂዶ ከ400 በላይ ሰላማዊ ዜጎች ህይወታቸው ተቀጥፎአል። በወቅቱ የፈደራል ጉዳዮች ሃላፊ የነበረው አባ ጸሃይና ሌሎች ቱባ ቱባ የመከላኪያና የደህንነት ባለሥልጣናት እጃቸው እንደነበረበት ቢታወቅም እስከዛሬ ድረስ አንዳቸውም ለፍርድ አልቀረቡም። ከ1996ቱ ጭፍጨፋ በተጨማሪም በክልሉ የሚካሄደውን የመሬት ቅሚያ የተቃወሙ፤ ከአያት ቅድሜ አያቶቻችው የወረሱትንና እትብታቸው ከተቀበረበት በሃይል አንፈናቀልም ያሉ በርካቶች ተገድለዋል ፤ ተደብድበዋል፤ ለእስርና ለስደት ተዳርገዋል። ከእስርና ከስደት ያመለጡ በርካቶችም በገዛ መሬታቸው ለአዳዲሶቹ ባለሃብቶች ጭሰኛ ሆነዋል አለያም ለጎዳና ተዳዳሪነት ተዳረገዋል። ይህ ሁሉ ግፍና መከራ አልበቃ ብሎ ከሰሞኑ ደግሞ "ማንነታቸው ያልታወቁ" የተባሉ ታጣቂዎች ከጎሬቤት ደቡብ ሱዳን ድንበር ተሻግረው ከ208 በላይ የኑዌር ተወላጅ ወገኖቻችንን ጨፍጭፈው ወደመጡበት ተመልሰዋል። ከተጨፈጨፉት ወገኖቻችን ከሃምሳ በላይ የሆኑት ህጻናት ሲሆኑ ሴቶችና አቅመ ደካማ የሆኑ ሽማግለዎች ቁጥርም ቀላል አይደለም። 

ይድረስ ለመላ የኢትዮጵያ ህዝብ!!! ከወልቃይት ጠገዴ የጎንደር ህዝብ

719e1-tigray-after-1991_011012
ሰበር ዜና፡ እኛ የወልቃይት ጠገዴ የጎንደር አማራ ህዝብ የወያኔ ሴራዋን አውቀን ብንታገስም እንኳ በምታደርስብን ስቃይ ወደ ግጭት እንድንገባ በማድረግ ህዝባችንን ለመጨረስ ዝግጅት እያደረገች ነው!!! በዚህ ሳምንት በወልቃይት ጠገዴ በዳንሻ ከተማ የሚገኙ ሁለት የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች “ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ጎንደሬ አማራ ነው” ብላችሗል ተብለው ከትምህርት ገበታቸው ተባረዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በትምህርት ቤቱ የሚያስተምር አንድ የወልቃይት ጠገዴተወላጅ መምህር ገ/ፃድቃን ከተባለ ትግሬ የኬምስትሪ መምህር ጋር “ ወልቃይት ጠገዴ አማራ ነው” ብሎ ስለ ተከራከረው ብቻ ከትግራይ አስተዳደሩ ከፍተኛ ዛቻና ማስፈራሪያ እየደረሰበት ይገኛል።

የወያኔ መንግስት የጋምቤላ ወገኖቻችንን መገደል ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ነው ተባለ


በትናንትናዉ እለት የደቡብ ሱዳንና የኢትዮጵያ ወታደራዊ ከፍተኛ አመራሮች ተወያይተዋል!!
ዉይይቱ እጅግ የሱዳናዊያን ብቻ ነበር የሚመስለዉ ያሉት ዉስጥ አዋቂ መረጃችን….
ተቆርቋሪነታቸዉ ለሱዳናዊያን የሙርሌ ብሔር ወንጀለኞች የሆኑ ሁለት ወታደራዊ አመራሮች በተለየ መልኩ በድንበር ማስጠበቁ እና የድንበር ማካለሉ ስራን አስረግጠዉ አስቀምጠዋል

Monday, April 18, 2016

ኢትዮጵያዊነት ነው የሞተው!

(Dr. Bedilu Wakjira )
.
ሰሞኑን በጋምቤላ ክልል በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች አሳዛኝ ጭፍጨፋ ደርሶባቸዋል፡፡ የኮምኒኬሽን ሚንስትሩ አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ትላንት (እሁድ) ለሮይተርስ የዜና አገልግሎት በሰጡት መግለጫ የሟቾቹ ቁጥር 208 እንደደረሰና 79 ሰዎች እንደቆሰሉ፣ በርካታ ህጻናት ታፍነው እንደተወሰዱ፣ 2000 ገደማ የቀንድና የጋማ ከብቶች እንደተነዱ ተናግረዋል፡፡

Friday, April 15, 2016

ሰበር ዜና… የወያኔ ወታደራዊ አመራር መረጃ ይዘዉ ጠፉ.

በልኡል አለም
81f3357c-3679-4a2e-8ace-14d07b92e5a7ተግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን ወታደራዊ ደህንነት በከፍተኛ ሁኔታ እየፈለጋቸዉ ይገኛሉ በትዉልድ ኦሮሚያ የሆኑት ኮረኔል ንጉሴ በሰራዊቱ ዉስጥ በአስከፊ ሁኔታ የተንሰራፋዉን የዘር የበላይነት በመጥላት ሐገራችዉን ጥለዉ በሰላም ጎረቤት ሐገር ገብተዋል።
የ43ተኛ ክፍለ ጦርን አዘዞ ላይ ካፈረሱና ምንም አይነት ብረት ለበስ ወይም ሜካናይዝድ ጦር ላልነበረዉ የምስራቁ እዝ ቀብሪ ደሐር ላይ የሁለጠኛ ሜካናይዝድ ካቋቋሙ ወዲህ የተሰወሩት ኮረኔል ንጉሴ…..

Thursday, April 14, 2016

አስቸኳይ የሆነ የአቋም ለዉጥ በኢትዮጵያ በኩል እስካልተደረገ ድረስ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉብኝት እንደሚሰረዝ ማሳስጠንቀቂያ ተሰጠ


ክቡር አቶ አንዳርጋቸዉ ስጌ ለትግራዩ ነጻ አዉጭ ቡድን ደህንነት ቢሮ ከፍተኛ እራስ ምታት ሆኗል።
የተከበሩት የቀድሞ የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ በወያኔ እጅ በግፍ ተላለፈዉ ሲሰጡ የእንግሊዝ የደህንነት አካላት ያዉቁ እነደነበር እና የየመን የጸጥታ ሐይሎች እንዲሁም የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን በመተባበር እገታዉን እንዳካሄዱት ዛሬ ከብሔራዊ መረጃ ምንጭ ተገኝቷል።

ሰበር ዜና — አቶ አንዳርጋቸዉ ጽጌ ለትግራዩ ነጻ አዉጭ ቡድን ደህንነት ቢሮ ከፍተኛ እራስ ምታት ሆኗል

በልኡል አለም
Ato Andargachew Tsige, Ginbot 7የተከበሩት የቀድሞ የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ ለወያኔ በግፍ ተላለፈዉ ሲሰጡ የእንግሊዝ የደህንነት አካላት ያዉቁ እነደነበር እና የየመን የጸጥታ ሐይሎች እንዲሁም የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን በመተባበር እገታዉን እንዳካሄዱት ዛሬ ከብሔራዊ መረጃ ምንጭ ተገኝቷል።
የእንግሊዝ ከፍተኛ የደህንነት አባላትን ጨምሮ አጣብቂኝ ዉስጥ የከተቱት አንዳርጋቸዉ ጽጌ በአምነስቲ ኢንተርናሽናልና በሌሎች ሁለት ከፍተኛ ተደማጭነት ባላቸዉ የሰባዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች እንዲሁም በወላጅ አባታቸዉ የሚጎበኙ ሲሆን የተለያዩ የወያኔን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዲስኩር ያዘሉ መጽሐፎች፣ እና መጽሄቶች በተለይም የክቡሩን ታጋይ ሞራል በሚነካ መልኩ አንዳንድ አልባሌ ጽሁፎችን ያካተቱ መጣጥፎችም ሆን ተብለዉ እንዲሰጡት ቢደረግም በጀግናዉ አንዳርጋቸዉ ላይ እየታየ ያለዉ አልበገር ባይነት በወያኔያዊያን ላይ የበላይነቱን ይዟል።
በተልይም የደህንነት ቢሮዉ ሚስጥራዊና ልዩ ስብሰባ ያካሔደ ሲሆን የእንግሊዝ ባለስልጣናት እራሳቸዉን ከተጠያቂነት ባሸሸ መልኩ በተገላቢጦሹ ታጋይ አንዳርጋቸዉን እንድንፈታ እያስገደዱን ነዉ። “ሰባዊ መብት ጥሰቱ እስካልቆመና አንዳርጋቸዉ ጽጌ ካልተፈታ ወይም አስቸኳይ የሆነ የአቋም ለዉጥ በኢትዮጵያ በኩል እስካልተደረገ ድረስ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉብኝት እንደሚሰረዝ ማሳስጠንቀቂያ አዘል ትእዛዝ ተሰጥቶናል” በሚል አጀንዳ ተንተርሶ የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን ጭንቅ ዉስጥ ገብቷል።
እንዳይለቁት እሳት እንዳይዙት መአት!!!  ይሏል ይህ ነዉ!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

Wednesday, April 13, 2016

በኢትዮጵያ በአለም ደረጃ በጣም ውድ የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት እንደምታቀርብ ተገለጸ

Image result for internet


በኢትዮጵያ በአለም ደረጃ በጣም ውድ የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት እንደምታቀርብ ተገለጸ
ዜና (ሚያዚያ 5 ፥ 2008)
ኢትዮጵያ በአለማችን ካሉ ሃገራት መካከል የኢንተርኔት አገልግሎትን በጣም ውድ በሆነ ክፍያ በማቅረብ ግንባር ቀደም ሃገር ሆና መገኘቷን በጉዳዩ ዙሪያ ጥናትን ያደረገ አንድ የቴክኖሎጂ ተቋም ይፋ አድርጓል።
ይኸው የ120 ሃገራትን ታሪፍ በንጽጽር ያቀረበው ኑሚቢዬ የተሰኘው አካል በኢትዮጵያ ዝቅተኛ ፍጥነት ባለው የኢንተርኔት አገልግሎት ክፍያው የማይቀመስ መሆኑንም አመልክቷል።
የኢትዮ-ቴለኮም ባለስልጣናት ይህንኑ አገልግሎት ጨምሮ በቫይበር የሚደረግ የስልክ ጥሪ ልውውጥ ላይ ክፍያን ተግባራዊ ለማድረግ ምክክርን በማካሄድ ላይ መሆኑን ባለው ሳምንት ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።
በሃገሪቱ በብቸኝነት የስልክ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ኩባንያው በአገልግሎቱ ላይ አዳዲስ የቁጥጥር ስርዓቶችን ተግባራዊ ከማድረጉ ጎን ለጎን የተንቀሳቃሽ የእጅ ስልኮችንም ለመመዝገብ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።



ወያኔና ትግሬ


ወያኔና ትግሬ
መስፍን ወልደ ማርያም
ሚያዝያ 2008
አዳም በበደለ መድኃኔ ዓለም ካሠ፤ የተጠቀሰውን አባባል የማያውቅ ክርስቲያን ያለ አይመስለኝም፤ ለእስላሞችም ቢሆን አዲስ ነገር አይሆንባቸውም፤ አዳም ትእዛዝ ጥሶ ዕጸ በለስን በላና ተረግሞ ከገነት ወጣ፤ አዳም በደለ የሚባልበት ምክንያት ይህ ነው፤ አዳም በገነት ባካሄደው አብዮት የተነሣ የሰው ልጆች ሁሉ ከገነት እንደወጡ የሚቀሩ ሆነ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር አዘነ፤ በዚህም ምክንያት እግዚአብሔር ወልድ ከሰማየ ሰማያት ወረደና ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ እግዚአብሔር ይህንን በማድረጉ ሰዎች ከአዳም የወረሱት የጅምላ ኃጢአት ተሻረ፤ ከዚያ በኋላ ኃጢአት የግል እንጂ የጅምላ መሆኑ ቀረ፤ ይህ የሆነው መድኃኔ ዓለም የሰው ልጅን ከራሱ ጥፋት ለማዳን በመሰቀሉ ነው፤ ሃይማኖት ለመስበክ ሳይሆን የጅምላ አስተሳሰብ ቀና እንዳልሆነ እግዚአብሔር እንዳስተማረን ለማመልከት ነው፤ በዚህም መሠረት ፍትሐ ነገሥት ልጅ በአባቱ ወንጀል አይጠየቅም፤ አባቱም በልጁ ወንጀል አይጠየቅም ይላል፤ በአስተሳሰብና በፍትሕ ጉዳይ የሰው ልጅን የእድገት በር የከፈተው ይህ ነው፤ እያንዳንዱ ሰው የሚመዘነውና የሚፈረድለት ወይም የሚፈረድበት እሱው ራሱ በሠራው ነው፤ ይህ ቁም-ነገር ዛሬ በሠለጠኑ አገሮች ሁሉ ሕግ ሆኖ የሚሠራበት ነው፤ ወደማኅበረሰብ ደረጃ ሲወርድ ቁም-ነገሩ ሰፊውን ሕዝብ አዳርሷል ለማለት ያስቸግራል።

ዶ/ር መረራ ጉዲና ከአዲስ አበባ ኤርፖርት እንዳይወጡ ባይከለከሉ ኖሮ በአሜሪካ ሊያቀርቡት የነበረው ጽሑፍ

merara_gudina_vtim
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከአዲስ አበባ ፓስፖርትህ ዘይት ነክቶት ማሽን አላነበው አለ በሚል ተልካሻ ምክንያት ከአዲስ አበባ አየር ማረፊያ እንዳይወጡ መታገዳቸውን ዘ-ሐበሻ በወቅቱ ዘግባው ነበር:: ዶ/ሩ የአዲስ አበባውን አየር ማረፊያ የደህንነቶች ወከባ አልፈው ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ቢመጡ ኖሮ የሚከተለውን ጽሁፍ ቭዥን ኢትዮጵያ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ ያቀርቡ ነበር:: ዘ-ሐበሻ ይህ የዶ/ር መረራ ጽሁፍ ደርሷታል በፒዲኤፍ ያንብቡት::

Tuesday, April 12, 2016

ወያኔ መንግስት የኮምፒውተር መረጃዎችን መጥለፍ፣ መበርበር፣ መሰለል የሚያስችል ህግ አረቀቀ

መንግስት እንደፈለገ የግል የኮምፒውተር መረጃዎችን መጥለፍ፣ መበርበር፣ መሰለል፣ ኦን ላይን መፈለግ የሚያስችለውን ህግ አርቅቆ ለፓርላማ አቅርቦአል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ኮምፒውተር ወይንም የኮምፒወተር ስርዓት ምንነት ሲያብራራ በሶፍትዌር እና ማይክሮቺን ቴክኖሎጂ ላይ የተመሠረተ የዳታ ፕሮሰሲንግ፣ ክምችት፣ ትንተና፣ ስርጭት፣ ግንኙነት ወይንም ሌሎች ሂሳባዊ ወይንም አመክኖአዊ ተግባራትን የሚያከናውን ማንኛውም መሳሪያ ነው ይለዋል፡፡

Monday, April 11, 2016

የአቶ አባይ ፀሃየና የስኳር ኮርፖሬሽኑ ድራማ


ሟቹ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ, አባይ ፀሃይና ,መሰል ጓደኛሞቹ ተሰባስበው በስኳር ፋብሪካዎቹ ጀርባ ወያኔ በትግራይ ቁጥሩ እየጨመረ የመጣውን ትምህርት ጨርሶ ቁጭ ያለው ስራ አጥ ስራ ስለማስያዝና በተያያዥም በርከት ያለ የትግራይን ሰው ወደ አዲስ አበባ በስራ ምክንያት ማዘዋወር ስለሚቻልበት ለመምከር ነበር ጓደኛሞቹ ለስብሰባ የተቀመጡት ከብዙ የሃሳብ ፍጭት በኃላ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ከተሰብሳቢ ጓደኛቻቸው የተሰነዘሩትን ሃሳቦችና አስተያየቶች ጨምቀው ጠቅለል ያለ መሆን አለበት ያሉትን የራሳቸውን ጨምረው በፅሁፍ መልክ አቀረቡ ::

Saturday, April 9, 2016

የወያኔ ስርሃት ችግሮች እየገጠሙት እንደሆነ የብሪታኒያው ዘ-ጋሪድያን ዘገበ

12376295_1018502434888475_6231050438946837590_n
በኢትዮጵያ የፖለቲካ ልዩነቶችንና አመለካከቶችን በተገቢው ሁኔታ ሊስተናገዱ ባለመቻላቸው በሃገሪቱ ተቃውሞ ኣየተባበሱ መምጣቱን የብሪታኒያው ዘ-ጋሪድያን ጋዜጣ የተለያዩ መረጃዎች ዋቢ በማድረግ አርብ ዘገበ። በተለያዩ ክልሎች መጠኑን እያሰፋ የመጣው ይኸው ተቃዎሞ በኢትዮጵያ የፌዴራሊዝም ስርዓት አተገባበርና በዴሞክራሲያዊ የመብት ጥያቄዎች ላይ ጥያቄ አስነስቶ እንደሚገኝም ጋዜጣው አስነብቧል።

Friday, April 8, 2016

ትግሉ ሰፊ የምሁራን ተሳትፎ ይሻል! (አርበኞች ግንቦት 7)

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyኢትዮጵያ በበብዛትም ይሁን በጥራት በውጭው አለምም ይሁን በሀገር ውስጥ የሚኖሩ ብዙ ምሁራን ያፈራች ሀገር ነች። በጅጉ የሚያሳዝነው ግን በሀገሪቱና በሕዝቧ ችግር ላይ ሀሳብ ሲሰጡ ፣ ባደባባይ ሲከራከሩና ሲታገሉ የሚታዩት በጅጉ ጥቂቶች ናቸው። ርግጥ ነው ተከታታይ መንግስታት በምሁራን ላይ ያደረሱት ጥቃትና ማግለል ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም ምክንያት ብዙዎች መከራን ከህዝብ ጋር ከመጋፈጥ ይልቅ አጎንብሶ ማሳለፈን የመረጡበት ሁኔታ አለ። ቁጥራቸው ጥቂት ያልሆኑም ለግል ጥቅማቸው ቅድሚያ በመስጠት ከጨቋኝ ገዥዎች ጋር በመተባበር የሚሰሩ መኖራቸውም አይካደም። አብዛኛው ምሁራን በተለይም በብዙ የሀገሪቱ ጉዳይ ላይ ጠለቅ ያለ እውቀት ያላቸው ጭምር ሀገሪቱን ከገባችበት ማጥ ለማውጣት በሚደረገው ትግል ውስጥ እየተሳተፉ አይደለም። ይህ ዛሬ ባለው ችግርም ይሁን በታሪክ ፊት አሳዛኝ ነው።
ሀገራችን ዛሬ መስቀለኛ መንገድ ላይ ነች። የተማሩ ልጆቿ መላ እንዲመቱ በመጠየቅ ላይ ትገኛለች። ይልቁንም በሀገራችን ያለው ችግርና ሀገሪቱ እየሄደች ያለችበት መንገድና አቅጣጫ በተለይ ምሁራንን እንቅልፍ ሊነሰ ይገባል። ዕውነታው ከዚህም አልፎ የሀገሪቱን አሳዛኝና አደገኛ ሁኔታ ለመቀየር በሚደረገው ትግል ውስጥ ከፍተኛ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ግድ ይላል። የመንግስት ግፍና ሰቆቃ በበዛበትና የሀገራችን ሕልውና አደጋ ላይ በወደቀበት በአሁኑ ሰዓት ምሁራን ላለመሳተፍ ምክንያት ማቅረብ የማይችሉበት ወቅት ላይ ደርሰናል። እንደማንኛውም ሀገር ምሁራን የኢትዮጵያ ምሁራን በሀገራችን ውስጥ ሰላምና ዲሞክራሲ እንዲሰፍንና ፍትሕ የሰፈነበት ስርዓት እንዲመሰረት ሊሸሹት የማይገባ ትልቅ ሚና አላቸው።

ምን ዓይነት ድል? (ዶ/ር ታደሰ ብሩ የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር)

ምን ዓይነት ድል?
image
ሜጀር ጄኔራል አበበ ተክለሃይማኖት “የተገኘው ሰ,ላምና እድገት የሚንድ የአመራር ዘዴ በአስቸኳይ ይታረም” በሚለው ጽሁፉ ውስጥ እንደዋዛ ጣል ያደረጋት በህወሓቶች የምትዘወተር “ኢሕአዴግ ከሞት አፋፍ ተነስቶ፣ አንሰራርቶ ለድል የመብቃት ባህል አለው” የምትል ዓረፍተ ነገር አለች። ይህ አባባል በተለያዩ አቀራረቦች በጣም ብዙ ጊዜ ሰምቸዋለሁ።  ላተኩር የምፈልገው “ለድል መብቃት” የምትለዋ ሀረግ ላይ ነው። ለእንዴት ዓይነት ድል?
በነገራችን ላይ የሜ/ጄ አበበ ጽሁፍ ህወሓት ላይ ጥንቃቄ የበዛበት ልስላሴ ቢያሳይም በአጠቃላይ ሲታይ በጣም ጥሩና የተኙትን አንቂ ደወል ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ይህንን ደወል የሚሰሙ ጆሮዎች ኢህአዴግ የሚባለው ስብስብ ውስጥ ያሉ ግን አይመስለኝም። ወደ ጉዳዬ ልመለስ።

Thursday, April 7, 2016

“የጥናቱ ውጤት በ2003 ይቀርባል” አቶ መለስ

effort and midroc

ኢህአዴግን ወደ ኅብረ ብሔር ፓርቲ የማሸጋገር ሥራ እየተሰራ መሆኑንን ሃይለማርያም ደሳለኝ የአገሪቱን “ምሁራን” ባናገሩበት ወቅት ፍንጭ ሠጥተዋል። የዛሬ ሰባት ዓመት ከመስከረም 5 እስከ 7 ቀን 2001 ዓ.ም ሃዋሳ ተካሂዶ በነበረ የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባኤ አቶ መለስ ድርጅታቸው ወደ ብሄራዊ ፓርቲ ወይም አሃዳዊ ፓርቲ ስለመሸጋገሩ እየተጠና መሆኑንን ተናገረው በቀጣዩ ጉባኤ ሪፖርቱ እንደሚቀርብ ቃል ገብተው ነበር። ጥያቄው ዝም ብሎ የቀረበ ሳይሆን ታስቦበትና ከዚህ ቀደም የተሰጠውን መልስ በማስታወስ ነበር። ይህ የሚያሳየው አሃዳዊ ፓርቲ የመሆን ጉዳይ የዛሬ አለመሆኑን ነው።

ሰበር ዜና — ወያኔ ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 29 በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ላይ በዳንሻ ከተማ የጦርነት አዋጅ መርዙን ሲረጭ አምሽቷል

ከወልቃይት ጠገዴ ብጌምድር ፤ጎንደር ኢትዮጵያ
መጋቢት 29 /2008 አ/ም
በዛሬው  ቀን ወያኔ የዳንሻን ወልቃይት ጠገዴ ህዝብ በነገው ቀን ስብሰባ ካልወጡ ከባድ እርምጃ  እንደሚወስድ  አስጠነቀቀ። ነገ  መጋቢት 30  ሱቆች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ጣብያና ክሊኒኮችና ሁሉም  የሲቪል  ሰርቪስ  ቢሮዎች  ካላንደር  ሳይዘጋቸው በእነርሱ  ፈቃድ ብቻ  ነገ  እንዲዘጉ  ትእዛዝ  ካስተላለፉ  ብሗላ  በያንዳንድዋ  የዳንሻ  ከተማ ጥግ ልዩ  ልዩ የስድብና  ማስፈራሪያ  የተሞሉበት ትምክህታዊና ውዳቂ  መፈክሮች  የተጻፈባቸው  ጨርቆችና  አርቴፊሻል ላይቶች ዲኮር  አድርጎ “አንድም  የዳንሻ  ሰው  በነገው  ቀን በተዘጋጀው ስብሰባእንዳይቀር!”  በማለት  በተለየ  ሁኔታ ደግሞ  አንድም  በዳንሻ  የሚገኙትን   የወልቃይት  ጠገዴ ወጣቶች ሞባይሎቻችሁ ከቤቶቻችሁ  ጥላችሁ በስብሰባው  ባትገኙ ውርድ ከራሴ!!!”  በማለት በሶስት  መኪኖች  ሞንታርቦዎቹ  እስኪቀደዱ  ድረስ  እያስጠነቀቀ  እስከዚህችው  እስከ ምሽቱ 4:45 ከተማዋን እያመሳት ይገኛል። ውድ ወገኖቻችን እየደረሰብን ያለውን መከራና ስቃይ እባካችሁ ተረዱልን።
በሶስት  ሞንታርቦዎች  ጀሮአችንን  የሚያደነቁሩን  አንሷቸው  ፖሊሶችና ካድሬዎች  በአካል መስጊድ ድረስ ሄደው ሙስሊሞች እየሰገዱ ሳለ ምንም ኣይነት ስቅታ ሳይሰማቸው አጨብጭበው ካስቆሟቸው ብሗላ ነገ ከበሯቸውናየበአል ልብሳቸው ለብሰው እንዲወጡ እያስፈራሩ ሲናገሩዋቸው የመስጊዱን  በር  ከሚዘጋ  ከአንዱ ሙስሊም  ወገናችን ውጭ ሁሉም  በመስጊድ ሲሰግዱ የነበሩት  ሙስሊም  ወገኖቻችን  በንዴት ስግደታቸውን ሳይጨርሱ ፖሊሶቹንና ካድሬዎቹን ሳያናግሩዋቸው እዛው የመስጊዱ  ግቢ  ውስጥ ጥለዋቸው ሄደዋል።

Sunday, April 3, 2016

ኢሳት ወደ አየር ተመለሰ – ከኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን እና ሬዲዮ የተሰጠ መግለጫ

ESAT television new satelliteኢሳት ባለፉት ስድስት ዓመታት (ከሚያዚያ 2003 እ/ኤ/አ April 2010) ጀምሮ በኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ውጭ የኢትዮጵያውያን ከፍተኛ የመረጃ ምንጭ ሆኖ እያገለገል ይገኛል።ኢሳት በኢትዮጵያ ምድር እንዳይታይ ከሳተላይት ለማውረድ ስድስት ዓመታት ሙሉ በተደረገው የመንግስት ርብርብ 20 ያህል ሳተላይት ለመቀየር እና ተጨማሪ ወጪ ለማውጣት ተገደናል።ለሳተላይት አቅራቢ ኩባንያዎች የተማጽኖ ደብዳቤ በመጻፍ እና መደለያ በማቅረብ እንዲሁም ዋሺንግተን ፖስትን የመሳሰሉ ታዋቂ የምዕራብ ሚዲያዎች ጭምር እንደዘገቡት ኢሳት ላይ የሳይበር ጥቃት ቢሞከርም ሁሉንም ተቋቁመን ለ 6ኛው ዓመት ደርሰናል፥ ግባችን ዓመታት መቁጠር ሳይሆን ነጻነት በመሆኑ የኢትዮጵያውያን የዋይታ ድምጾች በደስታና ድል ሲመነዘሩ ለማየትና ለመስማት ተስፋም ሰንቀናል።

ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያነበዉ የሚገባ ከሕወሓት ጓዳ የወጣ ወሳኝ መረጃ – “አማራን ለመነጣጠል የተዛቡ ታሪኮችን መጻፍ”


(ከዚህ ቀደም ከጉራ ፈረዳ የተፈናቀሉ አማሮች፡ ፎቶ ፋይል)
(ከዚህ ቀደም ከጉራ ፈረዳ የተፈናቀሉ አማሮች፡ ፎቶ ፋይል)
ከታመነ ይህዓለም
ህወሐት የአማራን ህዝብ እንደገና በጎሳ ለመከፋፈል በትግርኛ ጽፎ ለሕወሐት አባሎችና በነርሱ ስር ላሉ ተጠርናፊዎች እያሰራጨው የሚገኘው አጭር እቅድን የውስጥ አርበኞች አደባባይ አውለውታል:: ትግረኛውንም ወደ አማርኛ እንዲተረጎም “ትንሳኤ ሃገር” አድርጎ ለሕዝብ ይፋ ሆኗል:: የትግረኛውን ከላይ – ከታች ደግሞ የአማርኛውን ትርጉም ያንብቡ::