Translate

Saturday, October 31, 2015

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የለሊቱ የቪኦኤ ሚስጥራዊ ጉባኤ (በአበበ ገላው)

በአበበ ገላው (ትርጉም በታኬ)
Tedros Adhanom and Ambassador Girma Birruበቅርቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኃኖም እና አምባሳደር ግርማ ብሩ በዩናይትድ ሰቴትስ አሜሪካ ዋሽንግተን ዲ.ሲ በሚገኘው የቪኦኤ ሬዲዮ ጣቢያ በሌሊት በድብቅ በመግባት ሕጋዊ ስልጣኑ ሳይኖራቸው ስለስርጭቱ ለጥቂት የድርጅቱ ሠራተኞች የኢዲቶሪያል መመሪያ ከሰጡ በኋላ በአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው አገልግሎት (ቪኦኤ) እና በህወሀት የበላይነት በሚመራው የኢትዮጵያ መንግስት መካከል ያለው የሻከረ ግንኙነት ያልተጠበቀ አቅጣጫ ይዟል፡፡ ስብሰባው በሚስጥር በተካሄደበት ጊዜ የአምባገነኑ አገዛዝ ባለስልጣኖች ለሬዲዮ ስርጭቱ ሰራተኞች ስለዜና አዘጋገብ፣ እንደዚሁም ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ ስለሚተላለፈው የስርጭት ጥራት ሁኔታ መመሪያ የመስጠት ሙከራ ያደረጉ ለመሆናቸው ከታመኑ ምንጮች በተገኙ መረጃዎች ተረጋግጧል፡፡

አይኔ አያየ እዚህ ዉስጥ አልገባም – መሠረት ሙሌ (ኤፍሬም ማዴቦ ከአርበኞች መንደር)

ኤፍሬም ማዴቦ ከአርበኞች መንደር
Patriotic Ginbot7 fighters
መብራቱን አጥፍቼዉ አልጋዬ ላይ የወጣሁት በግዜ ነዉ። አለወትሮዬ እንቅልፍ የሚባል ነገር በአይኔ አልዞር ብሎኝ ከጨለማዉ ጋር ፊት ለፊት ተፋጥጠናል። የነፋስ ሸዉታ እንኳን የማይሰማበት ደረቅ ሌሊት ነዉ። ጨላማዉ አይን ይበሳል። እቤቱ ዉስጥ ያለዉ ሰዉ ሁሉ ተኝቷል። ቀኑን በሠላም ላዋለኝ አምላክ ምስጋና ሰጥቼ ሌሊቱንም አደራ ብዬዉ ፀሎቴን ጨረስኩ። ያ ምቀኛ እንቅልፍ ግን አሁንም እንደከዳኝ ነዉ። ትንሿ አልጋዬ ላይ ግራ ቀኝ እያልኩ ተገለባበጥኩ። እንቅልፍ ተጎትቶ የሚመጣ ይመስል አሁንም አሁንም ላይ ታች እያልኩ አልጋዉ ላይ እራሴን ጎተትኩት . . . እንኳን እንቅልፍ ሊወስደኝ ጭራሽ አይኖቼ መርገብገባቸዉን ያቆሙ ይመስል ቀጥ ብለዉ ቀሩ። ከተጋደምኩበት ብድግ ብዬ መብራቱን አበራሁና ለመንገድ ከያዝኳቸዉ ሁለት መጻህፍት አንዱን አዉጥቼ ማንበብ ጀመርኩ። እኔ ላንብበዉ ወይ መጽሀፉ ያንብበኝ አላዉቅም። ጧት ስነሳ ግን “The Architecture of Democracy” የሚል መጽሐፍ ደረቴ ላይ ተለጥፎ ነበር።

Thursday, October 29, 2015

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ) በላንድ ክሩዘር መኪና ተሳፍረው ወደ አርባ ምንጭ ከተማ በፍጥነት ያመሩ የነበሩ 10 የፌደራል ፖሊስ አባላት ኮንሶ እና ቦረና መገንጠያ ድልድይ ላይ ከነመኪናቸው ሙሉ በሙሉ ተደመሰሱ፡፡


የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)
በላንድ ክሩዘር መኪና ተሳፍረው ወደ አርባ ምንጭ ከተማ በፍጥነት ያመሩ የነበሩ 10 የፌደራል ፖሊስ አባላት ኮንሶ እና ቦረና መገንጠያ ድልድይ ላይ ከነመኪናቸው ሙሉ በሙሉ ተደመሰሱ፡፡
====================================================
በትናንትናው ዕለት አመሻሽ ላይ አስሩ የፌደራል ፖሊሶች መጀመሪያ አንድ አይሱዙ የጭነት መኪና በኃይል በማስገደድ አስቁመው የተሳፈሩ ሲሆን መኪናው መንቀሳቀስ ሲጀምር "የጫንካቸውን ፖሊሶች አራግፍ አለያ ከነንብረትህ አብረህ ትጋያለህ!" የሚል የስልክ ማስጠንቀቂያ መልዕክት ለአሽከርካሪው በመድረሱ አሽከርካሪው መኪናውን አቁሞ ፖሊሶቹን "አልሄድም" ይላቸዋል፡፡ ቀጥሎም ፌደራል ፖሊሶቹ ሾፌሩን ለማንገራገር ሞክረው ትዕዛዛቸውን በቀላሉ ሊቀበል ባለመቻሉ ስልክ ተደዋውለው ሌላ ላንድ ክሩዘር መኪና እንዲመጣላቸው በማድረግ ተሳፍረው ጉዟቸውን ቀጥለው ኮንሶ እና ቦረና መገንጠያ ድልድይ ላይ ሲደርሱ ቅፅበታዊ ጥቃት ተከፍቶባቸው ከነተሳፈሩበት መኪና ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል፡፡
በተያያዘ ዜና ሙሉጌታ አባ፣ ፀጋዬ ገብረ ፃድቅ እና በኃይሉ ሲሳይ የተባሉ የህወሓት ጆሮ ጠቢዎችና የአካባቢው ቆራጭ ፈላጮች ፎቶግራፋቸው በማህበራዊ ሚዲያው መሰራጨቱን ተከትሎ ከትናንት ምሽት ጀምሮ አርባ ምንጭ ከተማ ከከዚህ ቀደሙ በባሰ ሁኔታ በፌደራል ፖሊስ ተጥለቅልቃ እየታመሰች ትገኛለች፡፡ 

Wednesday, October 28, 2015

(ሰበር ዜና) መምህር ግርማ ታሰሩ

Memeher-Girma
(ዘ-ሐበሻ) በአውሮፓ የተለያዩ ሃገራት በማጥመቅ ላይ ቆይተው ወደ ሃገራቸው የተመለሱት መምህር ግርማ ወንድሙ በአዲስ አበባ ፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የመምህሩ ቅርብ ሰዎች የሆኑ ታማኝ የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ:: እንደ ዘ-ሐበሻ ምንጮች ዘገባ ከሆነ መምህር ግርማ ወንድሙ ፈቃድ ሳይኖራቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም ተጠቅመው በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገር በማስተማር እና በማጥመቅ ሥራ ላይ ተሰማርተዋል በሚል በቤተክህነት በቀረበባቸው ክስ ነው የታሰሩት:: በአገልግሎታቸው የተነሳ በወንጀል እንደሚጠየቁ በፖሊስ እንደተነገራቸው የተገለጸው መምህር ግርማ በአዲስ አበባ ፖሊስ ቁጥጥር ሥር ላይ ውለው ምርመራቸው እንደቀጠለ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል:: ምንጮቻችን የሚያደርሱንን መረጃዎች ይዘን እንቀርባለን::

ዘ-ህወሀት በኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሀብ ማቆም ይችላልን? (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በአውዳሚ ረሀብ መካከል ተሰንጋ መያዟ ታላቅ ዓለም አቀፍ ሚስጥር ሆኖ ይገኛል፡፡Can the T-TPLF Stop the Famine in Ethiopia?
.. 1984-85 ወዲህ ለሁለተኛ ጊዜ የተከሰተ ታላቅረሀብ!
ባለፈው ሳምንት ግሎባል ፖስት/Global Post የተባለው የዜና ወኪል በርዕሰ አንቀጹ የመጀመሪያ ርዕስ በማድረግ እንዲህ የሚል ጥያቄ አቅርቧል፡
“ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ በአስከፊነቱ የመጀመሪያ የሆነውን ድርቅ ተጋፍጣ ትገኛለች፡፡ መንግስት በአሁኑ ጊዜ የተከሰተውን ረሀብ ማስቆም ይችላልን?”
ግሎባል ፖስት መንግስት ረሀቡን ማስቆም ይችላል ወይ የሚል ጥያቄ ያቀረበለት እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ ለሚጠራው የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ (ዘ-ህወሀት) ነው፡፡

Tuesday, October 27, 2015

አይ ስብሐት ነጋ – ከፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

በኢትዮጵያ ውስጥ ሥልጣን ሳይኖረው ባለሙሉ ሥልጣን፣ እውቀት ሳይኖረው ባለሙሉ እውቀት የሆነ ሰው ስብሐት ነጋ ብቻ ነው፤ እንዲያውም ከዚያም አልፎ ራሱን የቻለ ሉዓላዊ ነጻነት ያለው ግለሰብ ነው ለማለት የሚቻል ይመስለኛል፤ በዚህ ግለሰብ ላይ የማደንቃቸው ሁለት ነገሮች ናቸው፤ በሉዓላዊነቱ የተጎናጸፈውን ሥልጣን ሙሉ በሙሉ ይጠቀምበታል፤ ይቆጣኛል ወይም ይቀጣኛል ብሎ የሚፈራው የለም፤ ስብሐት ነጋ የሚፈራው ምንም ነገር የለም፤ ሁለተኛ በሉዓላዊነቱ ያለውን ሙሉ ነጻነት በሙሉ ልብ ይጠቀምበታል፤ ናስ በላይ ከበደ እንዳለው ‹‹የቅብጠት መዘላበድ›› ሊሆን ይችላል፤ ስብሐት ነጋ የተናገረው ነገር ትክክል ይሁን አይሁን ጉዳዩ አይደለም፤ ዋናው ነገር መናገሩ ነው።

በቅርቡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከጋዜጠኛነት ተማሪዎች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ሁለት ሰዎች ጽፈው አይቻለሁ፤ ዶር. በድሉ ዋቅጅራ በፋክት ላይ፣ ናስ በላይ አበበ በኢትዮ-ምኅዳር ላይ፤ ሁለቱም ሰዎች አልወደዱለትም ማለት ያንሳል፤ የሚወዱለትና የሚያጨበጭቡለት መኖራቸውም ሳይታለም የተፈታ ነው፤ ነገር ግን ስብሐት ነጋም ሆነ ደጋፊዎቹ አደባባይ ወጥተው ለመከራከር አይችሉም፤ ናስ በላይ አበበ እንደሚነግረን ‹‹አቶ ስብሐት ነጋ የውጭ ሰው እንዳይገባ ከተማሪዎቹ ጋር ተደራድረው ነበር የመጡት፤ ስለሆነም ነበር ከፍተኛ ጥበቃ አልፈን የገባነው፤›› ብቻውን ተናግሮ በጭብጨባ የሚሸኝበት መድረክ በመፈለጉ በከባድ ጥያቄም ቢሆን የሚያጣድፉት ሰዎች እንዳይኖሩ ማረጋገጡ በተማሪዎቹም ቢሆን ውሎ አድሮ ትዝብት ላይ ይጥለዋል።

የተቦርነ የፈራረሱ ቅኝቶች (ከአርአያ ተስፋማርያም)

ከአርአያ ተስፋማርያም
ወዳጄ ተቦርነ በተመለከተ ግልፅ ያልሆኑልኝ ነገሮችን አንስቼ በጥያቄ መልክ አቅርቤ ነበር። አንተም ለኔ ጥያቄ የሚሆን የመልስ ፅሑፍ ለጥፈህ አነበብኩት። የመለስክልኝ መልስ በጣም አስገርሞኛል፣ ግራም አጋብቶኛል። ያንተኑ ተረት በመዋስ “ማሞ ሌላ መታወቂያው ሌላ” ብየዋለሁ። ምክንያቱም ጥያቄዬን መመለስ ስላልቻልክ ወይም ስላልፈለክ እኔን በመሳደብ ጥያቄውን ለማድበስበስ ስትሞክር ነበር። ሃሳብን በሃሳብ መርታት ሲቃትህ ሃሳቡን ያቀረበውን ግለሰብ የማጥቃት የተባለ የክርክር ግድፈት ወይም ሎጂካል ፋለሲ ነው። ምን አልባት ጥያቄዬን ካልተረዳኸው ደጋሜ ላንሳው።
ዘረኛ፣ ኣምባገነንና ሙሰኛ የሆነው የኢህአዴግ መንግስት ህዝባችንን ከፍላጐቱ ውጭ በሀይል፣ በማስፈራራትና በዘር በመከፋፈል እየገዛ 24 አመታት አለፈ። ይህ መንግስት የስልጣን ዘመኑ እንዲቀጥል ህዝቡን በዘር መከፋፈል፣ በሀይል ማፈንና አዲሱ ትውልድ በተለያዩ የማይረቡ ጉዳዮች ማደንዘዝ ዋና አላማዬ ነው ብሎ እየሰራ ይገኛል። ለብዙ ኢትዮጵያዊያን ሞት፣ እስራት፣ ግርፋት፣ ድህነትና ስደት ተጠያቂ ከሆነው ከዚህ መንግስት ጋር የጥቅም ተካፋይ ሆነው ስልጣኑ እንዲረዝም በገንዘባቸውና በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ከሚረዱት ሰዎች አንዱ ሼኽ አልሙዲ ናቸው። ሼኹ በኢትዮጵያ ፖለቲካ በፈፀሙት ደባ፣ የሀገሪቱን ሃብት በመበዝበዝ የሃገራችንን ባህልና ወግ የሚያናጋ የማህበራዊ ቀውስ በህብርተሰቡ ውስጥ በማምጣት የሚጠየቁ ሰው ናቸው።
ከላይ እንደጠቀስኩት የዚህ መንግስት ዋና አላማው ህዝቡን ከፋፍለህ መግዛት ብቻ ሳይሆን ትውልዱን ስለሃገሩ ታሪክ፣ ስለማንነቱ፣ ስለሰብዓዊና ዴሞክራሲ መብቶቹ እንዳያውቃና እንዳይጠይቅ ማደንዘዝ ነው። ለዚህ አላማ መሳካት የፖለቲካ፣ የታሪክ፣ የፍትህ፣ ፍልስፍናና የማንነት ጥያቄ የማያነሱትን እንዲሁም ህዝብ እንዲነቃ የሚያደርጉትን የመገናኛ ብዙሃን እየዘጋ፣ ሽብርተኛ እያለ ጋዜጠኞችንም እያሰረ፣ እያሸማቀቀ፣ ከሀገር ያሰድዳል። በተቃራኒው ደግሞ ህዝቡ ከሀገሩ ጉዳይ ጋር እንዲፋታ የፖለቲካም ሆነ የመብት ጥያቄ ሲያነሳ የተባለውን አድራጊ፣ የተጠየቀውን ፈፃሚ ይሆን ዘንድ እንደ ሰይፉ ፋንታሁን አይነት ትውልዱን የሚያደነዝዙ ዝግጅቶችንና መገናኛ ብዙሃንን “የመዝናኛ ፕሮግራም” በሚል ስም ይለፈልፋል።
አነተ ገለልተኛ እያልክ የምታወድሰው ጓደኛህ ሰይፉ ፋንታሁን ይህንን የኢህአዴግን አላማ ግንባር ቀደም አስፈፃሚ ከመሆኑ በተጨማሪ አሁን በስልጣን ላይ ያለውን አምባገነን መንግስት የሚደግፍ ካድሬ መሆኑን አገር ያውቃል። ከዚህ በተጨማሪ ሰይፉ የኢሃዴግ መንግስትን እድሜ ለማርዘም ሌት ተቀን የሚለፉትና የአገርን ሃብት ያለአግባብ የሚዘርፉት የሼኹ ሎሌ ነው። በቅርቡ በሸራተን ሆቴል ሲያገባ የሰርጉን ወጪ ሙሉ በሙሉ በሼኹ የተሸፈነለትም በዚሁ የኢህአዴግ ካድሬነቱና ታማኝነቱ የውለታ ምላሽ ነው። ከሼኹና ከገዢው ፓርቲ ጋር አልተባበርም ያሉና ከተፅዕኖ ውጭ የሆኑ አርቲስቶች ፈተና ሲገጥማቸው አይተናል። ህዝብ የጀግንነት ክብር ከሰጣቸው ታማኝ በየነና ቴዲ አፍሮ ይጠቀሳሉ።
ኢ.ሴ.ኤፍ.ኤን ከኢህአዴግና ከሼኽ አልሙዲ ተፅዕኖ ራሱን አላቆ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በመስራቱ ምን ያክል የህዝብ ድጋፍ እንደነበረውና ውጤታማ እንደነበረ አይተናል። እኔ ለአንተ የማቀርበው ጥያቄ የሚነሳው እዚህ ላይ ነው። እዚህ አሜሪካ አላሙዲ ከፈጠሩት የስፖርት ፌዴሬሽን ጋር የተባበሩትን አርቲስቶች እያወገዝክና ሌላ ስራ እንዳይሰሩ እያሳደምክ፣ በአንፃሩ ቀንደኛ የገዥው ፓርቲ ካድሬና የሼኹ ወዳጅ በመሆን ከኢትዮጵያ ህዝብ ከተዘርፈው ገንዘብ ተካፋይ የሆነው ሰይፉ ፋንታሁንን የአንተ ጋዷኛ በመሆኑ ብቻ አላሙዲ በሸራተን ደግሰው ሲድሩት ለምን ለማውገዝ ተሳነህ?..ማውገዝ እንኳ ቢቀር የሼኹ ሎሌ የሆነው ሰይፉን በምን መለኪያ ገለልተኛና በእመነቱ የሚፀና ለማለት ደፈርክ?.. ወይም ገለልተኛነትና በእምነት መፅናት ምን እንደሆኑ አታውቅም! አለበለዚያ ለአንተ ገለልተኛነትና በእምነት መፅናት ማለት ከአንተ ጋር የሚመሰረት ጓደኝነት ነው ማለት ነው። ሌላው ጥያቄ እዚህ አሜሪካ አገር ከአልሙዲ ጋር የተባበሩትን አርቲስቶች ከተቃወምክ አዲስ አበባ ላይ ከዚያው ግለሰብ (ሼኹ) ጋር የሚተባበሩትንና የቅርብ ወዳጅ የሆኑትን ሰዎች ማንቆለጳጰስ እንዴት ትችላለህ?..በተጨማሪ በአላሙዲ የሚረዳውን ፌዴሬሽንና ሸራተን ለየብቻ እንደሆኑ አድርገህ ለመግለፅ ሞክረሃል። እጅግ አስቂኝ ነው።ሁለቱም በሼኹ የሚዘወሩ ናቸው!
ከአምባገነኑ መንግስት ኢህአዴግና መንግስትን ከሚደግፉት እነሼኽ አላሙዲ ጋር መተባበር አይገባም ካልክ አቋምህ ወጥ ሊሆን ይገባል። አዲስ አበባም ሆነ አሜሪካ፣ ሰርግም ሆነ ስፖርት ጓደኝነት ኖረም አልኖረ፣ የግል ጥቅም ተገኘም አልተገኘ፣ አቋምህ ወጥ መሆን ይገባዋል። ስትቃወም፣ ስትደግፍ፣ ወጥ የሆነ አቋም ይኑርህ!
በእነኚህ ጉዳዮች ላይ የምታንፅባርቀው ወጥ ያለሆነ አቋም ሳስብ አንድ ጥንታዊ የቻይና ተረትን አስታወሰኝ። ሰውዬው በመንደሩ ውስጥ ሱቅ ከፍቶ ጦርና ጋሻ አንድ ላይ ይሸጣል። የሚገርመው ግን ጦሩን ሲያሻሽጥ “ሁሉንም ነገር ይበሳል” እያለ ሲሆን ጋሻውንም ሲያሻሽጥ “ምንም ነገር አይበሳውም” እያለ ነበር። አንተም፣ ያንተም ጓደኛም ሰይፉ ፋንታሁን ከአልሙዲ ተሻርኰ እየሰራና ሸራተን ሰርግ ሲደገስለት እያየህ ገለልተኛና በእመነቱ የሚፀና ብለህ ታወድሰዋለህ! አሜሪካ አገር ያሉ አርቲስቶች ከአልሙዲንና አላሙዲ ከፈጠሩት ፌዴሬሽን ዝግጅት ላይ ሲዘፍኑ ደግሞ “ባንዳና ከሃዲ” ብለህ ታወግዛለህ፤ እንዴት ነው ነገሩ?..የባንዳነትና የኢትዮጵያዊነት መለኪያው የአንተ ፍቃድና ጓደኝነት ሆነ እንዴ?..ለነገሩ የአንተን የአቋም መዘባረቅ በተመለከተ ግራ የሚያጋቡኝን አንድ ሁለት ነገሮች ልጠቃቅስልህና ወደ ዋናው ሃሳቤ ልመለስ። ድምፃዊ ቴዴ አፍሮ ከአልሙዲ ጋር ላለመስራት ወስኖ የኢትዮጵያ ህዝብ ጀግና እያለ ሲወድሰው ኢህአዴግ ደግሞ እንደጠላት ሲያዋክበው በነበረት ጊዜ አንተም ከሰይፉ ጋር ሆነህ ቴዲ አፍሮን በማዋከቡና የድምፃዊውን መልካም ስም በማጠልሸት ዘመቻ ላይ ከሰይፉ ጋር ተሳታፊ ነበርክ። ሁለተኛ የሰይፉን በመዝናኛ ስም ህዝብ የማደንዘዝ ተግባር ላይ አካልና አጋር ነበርክ። አንተ የእኔን የትላንት፣ የዛሬና የነገ አቋም ለመጠየቅ አንዳችም ማስረጃ ባይኖርህም እኔ ግን እነዚህንና ሌሎች ለጊዜው የማልገልፃቸውን ስህተቶችህን እያወቅኩ ኢትዮጵያዊነትህን አልተጠራጠርኩም።

Sunday, October 25, 2015

“ዘመድነህ ንጋቱ የኩባንያው ሳይሆን የህወሃት አገልጋይ ናቸው”

ዓለምአቀፉ ኧርነስትና ያንግ ኩባንያ ጉዳዩን እንዲመረምር ተጠየቀ

E&Y


የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በሚገዛት ኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ስም የኧርነስትና ያንግ የተሰኘውን የንግድ ሒሳብና ኦዲት ሥራ የሚያከናውን ኩባንያ ከፍተው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ዘመድነህ ንጋቱ በኦባንግ ሜቶ ለዓምአቀፉ የኧርነስትና ያንግ ኩባንያ የሥራ ኃላፊዎች አቤቱታ ቀረበባቸው፡፡

Friday, October 23, 2015

የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንደሌሉ ገለፀ (ነገረ ኢትዮጵያ)

• ‹‹የስርዓቱን ሽፍትነት ያመላክታል›› 3ኛ ተከሳሽ አቶ ደናሁን ቤዛ
• ‹‹የሚቀርብልን ምግብ ለእንሰሳትም መቅረብ የማይገባው ነው›› 2ኛ ተከሳሽ አቶ አሸናፊ አካሉ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
Ato Andargachew Tsige, Ginbot 7በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ -5ኛ መዝገብ ለተከሰሱት አቶ አሸናፊ አካሉ (2ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ደናሁን ቤዛ (3ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን (4ኛ ተከሳሽ) እና አቶ አንሙት የኔዋስ (5ኛ ተከሳሽ) በመከላከያ ምስክርነት የተጠቀሱት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደሌሉ ማረሚያ ቤቱ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛው ወንጀል ችሎት በላከው ደብዳቤ ገልፆአል፡፡ 19ኛ ወንጀል ችሎት ሀምሌ 29/2007 ዓ.ም የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸውን ለምን እንዳላቀረበ እንዲያብራራ፣ እንዲሁም ለምስክርነት እንዲያቀርብ ለዛሬ ለጥቅምት 12/2008 ዓ.ም ለአራተኛ ጊዜ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበር ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው ቃሊቲ እንደሌሉ በደብዳቤ አሳውቋል፡፡

እናመሰግናለን! የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

እናመሰግናለን
Thank You! Zone9 bloggers
በድንገት ከያለንበት ተይዘን እንደታሰርነው አፈታታችንም ግራ የሚያጋባ ነበር፡፡ ተመሳሳይ ክሶች ቀርበውብን እያለ ግማሾቻችን ‹ክስ ተቋርጦላችኋል› ተብለን ተፈታን፣ ግማሾቻችን ደግሞ ‹ነፃ ናችሁ› (ከሳሽ በነፃነታችን ላይ ይግባኝ መጠየቁ እንዳለ ሁኖ) ተብለን ይሄው ወጥተናል፡፡ ቀሪ ክስ ይዘን በዋስ ወጥተን እየተከራከርንም ያለን አለን፡፡ በዚህ ሁሉ መሃል የሁላችንም ዕምነት ግን አንድም ቀን ሊያሳስረን የሚገባ ወንጀል አለመፈፃችን ማመናችን ነው፡፡ መፈታታችን ጥሩ ሁኖ፤ መታሰር በፍፁም የማይገባን ነበርን፡፡ መፃፋችን እና ሕግ እንዲከበር መጠየቃችን ሀገሪቱ አገራችን እንድትሻሻል እና ሁላችንም ዜጎች የተሻለ ህይወት አንዲኖራቸው ከመሻት ባለፈ ሌላ ነገር አልነበረውም/የለውም፡፡ ነገር ግን ይህን በማድረጋችን ተገርፈናል፣ ተዘልፈን-ተሰድበናል፣ ታስረናል ተሰደናልም፡፡ ይህ በፍጹም አይገባንም ነበር፡፡

Thursday, October 22, 2015

“ከቤት ኪራይ ባሻገ…” (ተወልደ “ተቦርነ” በየነ)

ተወልደ (ተቦርነ) በየነ
Teborne Beyene Ethiopian journalistሰሞኑን ጋዜጠኛ አርአያ ተ/ማርያም አንዲት አጭር ማስታወሻ በገጹ ላይ ከትቦ ተመለከትኩ። ጋዜጠኛ አርአያ በዲሲና እና አከባቢዋ በሚገኙ ጉራንጉሮች እየቃረመ የሚያስነብበን የተለያዩ ገጠመኞች ናቸው። እርግጥ አብዛኞቹ በግለሰብ ማንነትና ስብእና ያተኮሩ ቢሆንም በሀገረ አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጲያውያን ሌላኛውን ገጽታ ለማሳየት ይጠቅማሉ ። በተለይ ሀገራችንን በወያኔ ተቀምተን ስደትን እንደአማራጭ የወሰድን ኢትዮጲያውያን “ትልቁን – ስዕል” እንዳንረሳ ከእነዚህ ውድቅዳቂ ገጠመኞች ማወቅ እንደሚጠቅመን አስባለሁ። ጋዜጠኛ አርአያም በአደገኛ ቦታዎች እየተሹለከለከ የሚያቀርበውን “ግለሰባዊ” ታሪኮች ቢገፋበት የሚያስከፋ አይደለም። እርግጥ አብዛኛው ሰው “የመንደር ወሬ” እያለ ቢያጣጥለውም እኔ ግን ከምንም ይሻላል የሚል አስተያየት አለኝ። አንዳንዶች ደግሞ “አርአያ አልቆበታል” ሲሉ ይደመጣሉ። ይህም ቢሆን ምላሹ ያለው ራሱ ጋዜጠኛው ጋር ስለሆነ ገፍቼ ልከራከር አልችልም።
በሌላ በኩል ሀገሩን በጥቂት የወያኔ ጉጅሌውች የተቀማው አብዛኛው ኢትዮጲያዊ ጋዜጠኛው ከቃረማቸው አከባቢዎች ውሎ የሚያድር አለመሆኑን መገንዘብ ያሻል። በሀገራቸው የመስራት እድል የተነፈጋቸው ኢትዮጲያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ ኑሮን ለማሸነፍ የሚተጉ መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል። በሀገር አሜሪካን የኢትዮጲያውያን አንዱ መታወቂያም የስራ ትጋታቸው እና ፍላጎታቸው መሆኑ ምስክር የሚያሻው አይደለም። በመሆኑም የዋሽንግተን ዲሲ ደቡባዊ ምስራቅ የሚገኙ አደገኛ ቦታዎች የሚውሉና የሚያዘወትሩ ጥቂት ኢትዮጲያውያን በመሆናቸው ብዙሃንን እንደማይወክሉ መገንዘብ ያሻል።

Monday, October 19, 2015

የኢትዮጵያና የኤርትራ መጻሔ ዕድልና ተስፋ (ኃይለገብርኤል አያሌው)

ከኃይለገብርኤል አያሌው
Ethiopia and Eritrea
የኢትዮጵያና የኤርትራ አንድነት በተካሄደው እልህ አስጨራሽ ጦርነት ከተበጠሰ በሗላ እንደ ሁለት ሃገርና እንደ ሁለት ሕዝብ የመሆን ታሪካዊ ሁኔታ ቢፈጠርም በደም ፤ በባህል ፤ በታሪክና ሃይማኖት በሁልንተናዊ መስተጋብሮች የተቆራኘው የነዚህ ሕዝቦች ሕልውና በጥብቅና በቅርብ ተሳስሮ ያለና ወደፊትም የሚኖር በመሆኑ እንደ ሌሎች ሃገር ሕዝቦች ተለያይቶና ተራርቆ ሊቀር ባለመቻሉ አበው ‘’የሞትንም እኛ የገድልንም እኛ’’ እንዳሉት ከሁለቱም በኩል ባሉ ቀና አሳቢዎች ድልድይነት የሻከረውን ግንኙነት ለማደስ የሚደረገውን ሙከራ በበጎ ጎኑ የማይመለከቱ ሃይሎች ተበራክቶና ተጽኖዐቸው አይሎ በመቆየቱ በአካባቢው ጥቅም ያላቸው ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ታክሎበት ፤ ኢትዮጵያን የተቆጣጠርው የሕወሓት ሴራ ተጨምሮበት ፤የአንደነት ሃይሎች ስልት የራቀው ፖለቲካና ግልብ ፕሮፓጋንዳ ተደማምሮ ሁለቱን ህዝቦች ለማቀራረብ በጥቂት ወገኖች የተጀመረው መልካም ጥረት የሚፈለገው ያህል ባይራመድም ይህን ውጥን ጅማሮ በዘላቂነት ማጠናከሩ ለሁለቱም ሃገር ሕዝቦችና ለአካባቢው መረጋጋት ጉልህ ሚና የሚኖረው መሆኑ ሊሰምርበትና የተጀመረውን የማቀራረብና የመወያየት ጅማሮ ሁሉም ድጋፉን ሊቸረው የሚገባ ጉዳይ ነው።

የአርበኞች ግንቦት 7 ሪከርድ የሰበረ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሚኒሶታ * ነአምን ዘለቀ አርበኞች ግንቦት 7 መንፈስ ነው አሉ (ሪፖርታዥ)


የአርበኞች ግንቦት 7 ሪከርድ የሰበረ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሚኒሶታ * ነአምን ዘለቀ አርበኞች ግንቦት 7 መንፈስ ነው አሉ (ሪፖርታዥ)
“የኤርትራ መንግስት ከራሷ ጋር የታረቀች ጠንካራ ኢትዮጵያ እንድትመሰረት ይፈልጋል”
“ሁሉንም ፖለቲካ ሃይሎች ያካተተ የሽግግር ሂደት ይኖራል”
“የወደብ ጥያቄን በተመለከተም ወደፊት በድርድር/በሰጥቶ መቀበል የሚፈታ ይሆናል እንጂ አሁን የትግሉ አጀንዳ መሆን የለበትም”
“የመረጃ ትንሽ የለውም… መረጃ አይናቅም”
(ዘ-ሐበሻ) በሚኒሶታ ትናንት ማምሻውን ለአርበኞች ግንቦት 7 ገቢ ማሰባሰቢያ የተደረገው ዝግጅት በታሪካዊነቱ እንደሚቀመጥ የሚኒሶታ ነዋሪዎች አስታወቁ:: በሚኒሶታ ታሪክ ለአንድ የፖለቲካ ድርጅት በአንድ ቀን 78 ሺህ ዶላር በላይ ሲሰበሰብ የትናንቱ የመጀመሪያው ነበር::

Sunday, October 18, 2015

“ድል ለአርበኞች ግንቦት 7!” “ሞት ለወያኔ!” የሚሉ ፅሁፎች በኢትዮጵያ ከተሞች እየተሰራጩ ነው

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ
“ድል ለአርበኞች ግንቦት 7!” “ሞት ለወያኔ!” የሚሉ እና ሌሎች ፅሁፎች በአርባ ምንጭ ከተማ በዋና ዋና ቦታዎች ላይ በብዛት ተለጥፈው ታዩ፡፡
Patriotic Ginbot7 flyers distributed in Ethiopian cities
ጠንከር ያለ የፀረ-ህወሓት ህዝባዊ ትግል እየተካሄደባቸው ከሚገኙት የኢትዮጵያ አካባቢዎች አንዱ የአርባ ምንጭ ከተማ መሆኑ ይታወቃል፡፡ጀግኖች የአርባ ምንጭ ወጣቶች በከተማዋ ውስጥ ተደራጅተው ከፍተኛና ያልተቋረጠ የነፃነት ተጋድሎ በማድረግ አንድነትንና ዴሞክራሲን ለማምጣት ደጋግመው የህይወት ዋጋ ሲከፍሉ ከመቆየታቸውም ባሻገር ከሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለየ ሁኔታ በረሃ እየወረዱ የትጥቅ ትግሉን መቀላቀላቸውን አሁንም በአስደማሚ ሁኔታ ቀጥለውበታል፡፡ ከአንድ ሰፈር ብቻ ከ15 በላይ ወጣቶች አርበኞች ግንቦት ሰባትን ተቀላቅለው በከፍተኛ እልህ፣ ሞራል እና ወኔ በትግል ላይ ይገኛሉ፡፡

መንግስት ኢኮኖሚው ውድቀት ላይ መሆኑን አመነ (ነገረ ኢትዮጵያ)

• የኢኮኖሚ መዋቅሩ ከሳህራ በታች ከሚገኙ ሀገራትም ያነሰ ነው
• የወጪ ንግድ ገቢ እና የገቢ ንግድ ክፍተት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል
• ለውጭ ገበያ የቀረበው አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና፣ ሰሊጥና የጥራጥሬ ሰብሎች መጠን በእቅዱ ከተያዘው በእጅጉ ያነሰ ነው
• ለውጭ ይቀርባል ተብሎ ከታቀደው ቡና የቀረበው ሩቡ ብቻ ነው
• መስራት የሚቻለውን ያህል የልማት ሥራ ሳይሰራ ቀርቷል
• ሥራ አጥነት በከተማ ብቻ ሳይሆን በገጠር አካባቢዎችም ሰፊ ችግር ሆኗል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ላለፉት 10 አመታት ኢትዮጵያ 11.2 በመቶ በማደግ በዓለም ፈጣን እድገት እያሳዩ ከሚገኙ ጥቂት ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነችና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት ጋር ልትመደብ እንደሆነ ሲናገር የነበረው ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የኢኮኖሚ ውድቀት እንዳጋጠመው አመነ፡፡ የብሔራዊ የፕላን ኮሚሽን በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም የሁለተኛውን አምስት አመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ (ከ2008-2012 ዓ.ም) ላይ ለመወያየት ያዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ እንደሚያሳየው በተለይም መንግስት ለኢኮኖሚው አንቀሳቃሽ ሞተር ነው የሚለው የግብርና ዘርፍ፣ የውጭ ንግድና የማኑፋክቼሪንግ ኢንዱስትሪው ውድቀት አጋጥሞታል፡፡

Tuesday, October 13, 2015

የኢትዮጵያ መንግሥት ገመና – ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ (ከዝዋይ እስር ቤት)



በዚህ አውድ ለማቅረብ የተገደድኩበትን ዘግናኝ ታሪክ፣ ወደር በሌለው አስከፊነቱ የተነሳ ለንባብ ባላበቃው በወደድኩ ነበር፡፡ ግና! ይህ መንግስታዊ የጭካኔ ተግባር፣ ዛሬም በምስኪን ዜጎች ላይ እየተፈፀመና ብዙዎችን ሰለባ እያደረገ በመሆኑ ህዝቡ ይህን ሊሸሸግ እየተሞከረ ያለውን መከራ ተረድቶ ሥርዓቱን በአደባባይ ዓመፅ “ሃይ!” ይል ዘንድ ትርክቴን ለማጠናቀር ተገድጄያለሁ፡፡ ለእስር ያበቃኝ የጋዜጠኝነት ሙያዬም ተጨማሪ ዕዳ ጭኖብኛል፡፡
“ጄል-ኦጋዴን”
ጄል ኦጋዴን በሱማሌ ክልል ርዕሰ-መዲና የሚገኝ፤ ለ800 እስረኞች ታቅዶ በ1992 ዓ.ም የተገነባ እስር ቤት ነው፡፡ የግቢውን ዙሪያ ከከበበው አጥር በግምት 15 ሜትር ፈንጠር ብሎ ሌላ ተደራቢ የድንጋይ አጥር ተበጅቶለታል፡፡ እስከ ሚያዝያ 24 1999 ዓ.ም ድረስ እስር ቤቱ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ካሉ መሰል ማጎሪያዎች ብዙም የተለየ አልነበረም፡፡ በዚህ በተጠቀሰው ቀን የኦጋዴን ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) ታጣቂዎች፣ አቦሌ እና ሰንደሬ ወታደራዊ ካምፖችን ጨምሮ፣ በነዳጅ ዘይት ፍለጋ ላይ የተሰማሩ ቻይናውያን ባለሙያዎች መኖሪያ ሰፈር ላይ የሰነዘሩትን ከባድ ጥቃት ተከትሎ የፖለቲካ እስረኞች ብቻ የሚታጎሩበት እስር ቤት ከሆነ ወዲህ ግን በዋይታ የሚናወፅና በደም ጅረት የሚጥለቀለቅ ምድራዊ ሲኦል ለመሆን በቅቷል፡፡

Monday, October 12, 2015

“ወያኔዎችን አጥኗቸው፣ እወቋቸው“ ሙሉጌታ ሉሌ (በልጅግ ዓሊ)

በልጅግ ዓሊ
ደግ ደጉን ስናጣ ፣ ሃዘኑ መረረ
ሞት አምላኩ ከድቶት፣ ገሎት በነበረ።
የሠፈራችን ሙሾ አውራጅ
እነሆ ጋሼ ሙሉጌታ ዐረፈ። ከዚህ ምስቅልቅሉና ቅጥ አምባሩ ከወጣ ዓለም በአካል ተለየ ። ጋሼ ሙሉጌታ ከእንግዲህ የሃገሩን አፈር በሞቱ እንኳ ላይቀምስ ነው። ዛሬ የሰው ሃገር አፈር ለብሶ በዝምታ ማሸለቡን መርጧል። ሃገሩን እንደናፈቀ የተለያት ቢሆንም ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሸጋገር ትምህርት ሰጥቶን አልፏል።Ethiopian journalist Mulugeta Lule
የጋሽ ሙሉጌታን ማረፍ የሰማን ብዙዎቻችን ይህቺ ሃገር ከእንግዲህ አስተማሪ የሆነ ሰው ማን ቀራት? ብለን እንድናስብ አድርጎናል። ለሃገር በርካታ ትምህርት የሚሰጡ እንደ ተንቀሳቃሸ ቤተ መጽሐፍት የሚቆጠሩ አንጋፋ የሃገራችን ጠበብቶች በሞት እየተለዩን ነው። እንደ ፕሮፌሰር አሥራት፣ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንንና አምባሳደር ዘውዴ ረታን የመሳሰሉ ቱባ ቱባ የሰው ሃብቶች ማጣታችን የጎዳንን ያህል የጋሽ ሙሉጌታም ህልፈተ ሕይወት እንዲሁ እንደሚጎዳን አያጠራጥረንም ።

የኢትዮሚዲያው አብረሃ በላይ ወያኔነት በሙሉጌታ ሉሌ ሞት መነጽር ሲጋለጥ

ተስፋዬ ነጋ (ዋሽንግተን ዲሲ)
በውጭ አገር ማለትም በአሜሪካ፣ አውሮፓ፣ እስያ እና አውስትራሊያ ያሉ ኢትዮጵያውያን በአገራቸውና ህዝባቸው ላይ ሰለሚደርሰው ጭቆና፣ አፈና፣ ግድያና፣ እስራት የሚወያዩበት፣ ሃሳቦቻቸውን የሚካፈሉበት፣ መፍትሄዎችን የሚያንሸራሸሩበት በማህበራዊ ሚዲያና በድረ-ገጾች ላይ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ተቃዋሚም ሆነ ደጋፊዎች የተለያዩ አቋሞች የሚያራምዱ ድረ-ገጾችን መጎብኘታቸው የተለመደ ነገር ነው። ከነዚህ ድረ-ገጾች ውስጥ በሳል ጽሁፎችን በማውጣት የሚታወቀው አቶ አብርሃ በላይ በባለቤትነት የሚያስተዳድሩት ኢትዮጵሚዲያ (www.ethiomedia.com) ነው። በአገር ውስጥም ይሁን በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በወያኔ የጭቆና አስተዳደር የሚደርስባቸውን በደል፣ እስር፣ ጭቆና፣ ግድያና ወከባ በተመለከተ ለማንበብ የሚጎበኙት ድረ-ገጽ ኢትዮሚዲያ ነው ብል ያጋነንኩ አይመስለኝም። ይህን ስል በሌሎች ድህረ-ገጾችንና በማህበራዊ ሚዲያዎችን ሚና ማሳነሴ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ።
አቶ አብርሃ ከኢትዮጵያ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና፣ የውጭ ሚዲያ ጋዜጠኞች ኢትዮጵያን የተመለከቱ ወይም በኢትዮጵያ ላይ ተፅዕኖ የሚኖራቸውን መጣጥፎችንና ቪዲዮችን እየወሰዱ በድረገጻቸው በማተም ለአንባቢያንና ተመልካቾች ሲያደርሱ ቆይተዋል። ኢትዮጵያን የተመለከቱ አስተማሪ ትንተናዎች (የእርሳቸው ባይሆኑም) በድረ-ገጻቸው እያተሙ ሲያስነብቡን መቆየታቸው እሙን ነው። እኔ እስከማውቀው ድረስ ድረ-ገጹ በህወሃው መራሹ መንግስት የተገፉ የኢትዮጵያውያን ድምፅ በማስተናገድ በኩል የተወሰነ አስተዋፅኦ አበርክቷል፥ እያበረከተም ይገኛል እላለሁ።

Saturday, October 10, 2015

ነጻ አውጪ ግምባር አገዛዝ እንጂ መንግሥት አይመሠርትም

"ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!" ሰማያዊ ፓርቲ

tplf haile debretsion

ላለፉት 25 ዓመታት በነጻ አውጪ ግምባር ስም ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር “ኢህአዴግ” ብሎ በፈጠረው ስያሜ አገር በግፍ እየገዛ መሆኑ ሳያንስ በየአምስት አመቱ በሚያካሂደው “ምርጫ” የሚመሠርተው “መንግሥት” መፍትሔ ሊሰጥ እንደማይችል መድረክ አስታወቀ። ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሃብ የአገዛዙ ፓርቲ ተጠያቂ ነው ይላል።

ቅጥ ላጣው ሙስና “ተጠያቂ ነኝ” – ህወሃት

"ህወሃት/ኢህአዴግ ያመጣውን ሙስና ራሱ ይፍታው" - ሕዝብ

corrupt


ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት በተለይ በአዲስ አበባ ቅጥ ያጣውን ሙስናና ዘረፋ በተመለከተ በጠራው ስብሰባ አስቀድሞ በመቀሌው “ተጠያቂ ነኝ” በማለት እንዳመነው አሁን ደግሞ ነዋሪው ችግሩን ራሱ እንዳመጣው ራሱ ይፍታው ማለቱ ተነግሮዋል:: የሪፖርተር ዘገባ እነሆ:-

Wednesday, October 7, 2015

ለክቡር ከንቲባይዬ – ጉዳዩ፡- የመኖሪያ ቤት መገንቢያ ቦታ ስለመጠየቅ

Image result for homeክቡር ከንቲባ ‹‹በአዲሱ መንግስት›› ይዤዎታለሁ፤ የምትከተለዋን ማመልከቻዬን አጠናቀው ያንብቡልኝማ!
በኃይሉ ገ/እግዚአብሔር
ክቡር ሆይ! እንኳን ከስኬታማው ወደ ሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አሸጋገርዎ! እንኳን ለአዲሱ ዓመትም አደረስዎ! ኧረ እንኳንም ‹‹ለአዲሱ መንግሥት›› አደረስዎ!
ክቡር ሆይ የቤት አከራዬን በደል እና የቤት ኪራይ ጭማሪ፤ የኑሮ ውድነቱን የምቋቋምበት አቅም አጣሁ… ልልዎ ፈለግሁና ከአፌ መለስኩት፡፡ ከ አ ፌ! …እንዲህ ማማረር ስኬታማውን ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ማሳጣት ይሆንን? ስል አሰብኩና፣ በእውነት ነው የምልዎ ከአፌ መለስኩት፡፡
ክቡር ከንቲባዬ ኮንደሚንየም ከተመዘገብኩ ስንት ዓመት ሆነኝ መሰለዎ፡፡ መጪው ግንቦት ሲመጣ አሥራ አንድ ዓመቴ፡፡ ጊዜው እንዴት ይሮጣል ክቡር ከንቲባ፡፡ ‹‹ኮንደሚኒየም ከተመዘገባችሁ ወዲህ ጠግባችኋል!›› የሚለውን የአከራዮቼን የቃላት በትር ከነቤተሰቤ ችለን መኖር ከጀመርን አሥራ አንድ ዓመት ሆነን፡፡ እግዚኦ!

ኢትዮጵያ እንደ ጋና መሆን የማትችለው ለምንድን ነው? (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
በአደባባይ በይፋ አምናለሁ፡፡
በጋናውያን ላይ መንፈሳዊ ቅናት አድሮብኛል፡፡Why Can’t Ethiopia Become Like Ghana?
ባራክ ኦባማ የመጀመሪያ ጉዞውን ወደ አፍሪካ ባደረገበት ወቅት በአፍሪካ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ወዳላት እና የከፍተኛ የምጣኔ ሀብት ባለቤት ወደሆነችው ወደ ናይጀሪያ ለመሄድ አልመረጠም፡፡
በአሁጉሩ በምጣኔ ሀብት ደረጃዋ የሁለተኛነት ደረጃ ወደያዘችው የኔልሰን ማንዴላ ሀገር ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ አልመረጠም፡፡
እንደዚሁም ደግሞ ኦባማ የወላጅ አባቱ የትውልድ ሀገር ወደሆነችው ወደ ኬንያ ለመሄድ አልመረጠም፡፡
ዜጎችን በማጎሪያ እስር ቤት እያጋዘች አሳር ፍዳ በማሳዬት በአስከፊነቷ በምትታወቀው እና በአፍሪካ የሁለተኛነት ደረጃን ይዛ ወደምትገኘው ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ አልመረጠም፡፡ ቻይና በዓለም ላይ በአስከፊ ደረጃ ዜጎችን በማሰር የቀዳሚነቱን ደረጃ ይዛ ትገኛለች፡፡ ወይ ጉድ! አንድ ዓይነት ላባ ያላቸው ወፎች አብረው ይበራሉ እንዲሉ መሆኑ ነው፡፡

አብዱ ኪያር ዘንድሮ አንበሳ ሆኖ መጣ

ሄርሜላ አበበ ከልደታ
የራሳቸውን ግጥምና ዜማ ከሚሰሩት ጥቂት የሃገራችን ድምጻውያን ጋር በዋነኝነት ይሰለፋል:: ብዙዎች ደግሞ መድረክ ላይ ሲጫወት ልክ እንደ ሲዲው ኩልል አርጎ በመዝፈን ያደንቁታል:: ለጥቂት አመታት አዳዲስ ስራ ሰርቶ አልቀረበም ነበር :: ምክንያቱንም ሲገልጽ ትምህርት ቤት ገብቶ ሲማር በመቆየቱ እንደሆነ አስረድቷል::Abdu Kiar, New Song Anbessa (Black Lion)
በአሁኑ ሰአት ላይ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ትምህርት እራሱን አሳድጎ ሶፍትዌር ዴቨሎፐር ሆኖ በመስራት ላይ ይገኛል:: በቅርብ የሚያውቁት ሰዎች ስለሱ ሲናገሩ ሰው አክባሪ ግልጽ እና ጥርስ የማያስከድን በጣም ተጫዋች ሰው ነው ይሉታል:: እኔና በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ከሰይፉ ፋንታሁን ጋር ያደረገውን ቆይታ በኢቢኤስ ክተመለከትን በኋላ ከለፉና ከጣሩ ምንም የማይደረስ ነገር እንደሌለ ስላሳየን ወደነዋል አክብረነዋል ልባችን ውስጥም ልዩ ቦታ ሰጥተነዋል:: ከጥበቡ ውጭ ለእውቀት እንዲህ ያለ ስፍራ በመስጠቱና ከዝና ጋር ትምህርት ቤት ሄዶ ስኬታማ በመሆኑ እጅግ በጣም አድንቀነዋል ብዙም አስተምሮናል::

Sunday, October 4, 2015

የተራበች ኢትዮጵያ (አንተነህ መርዕድ)

ከአንተነህ መርዕድ
Hungry Ethiopiaበሞት አፋፍ ላይ ቀናቸውን በፀጋ የሚጠባበቁ የሰማንያ አምስት ዓመት ካናዳዊ አዛውንት የስቃይ ማስታገሻ መድሃኒታቸውን እየሰጠኋቸው እያለ “ከየት አገር ነህ?” ሲሉ ጠየቁኝ በደከመ አንደበታቸው። የተለመደ የነጮች ጥያቄ በመሆኑ እንደወትሮዬ “ከአፍሪካ ነኝ” አልኳቸው። ብዙዎቹ እያንዳንዱ አገርን ለይተው የማያውቁ ስለሆነ ለወትሮው በቂ መልስ ነበር። “ከአፍሪካ ውስጥ ከየትኛው አገር ነህ?” ሲሉኝ በዋዛ እንደማንላቀቅ ተገነዘብሁ። ብዙዎቹ አዛውንቶች አገሬን ስጠራላቸው “የአበበ ቢቂላ” ወይንም “የሃይለስላሴ አገር” በማለት በአድናቆት ታሪካችንን አጥርተው የሚያውቁ ስለሚያጋጥሙኝ ስለራሱ ታሪክ ደንታ በሌለው ትውልድ የሚሰማኝን ሃዘን ያቃልሉልኛልና “ኢትዮጵያዊ ነኝ” በማለት ፈካ ብዬ ነገርኳቸው። ራሱን ኢትዮጵያዊ ብሎ መጥራት በሚያሳፍረው፣ የማንነት ቀውስ ውስጥ የወደቀ በበረከተበት ወቅት ማንነታችሁን ተቀብሎ በሚያምን ሰው ፊት ማንነታችሁን ስትገልፁ ምን ያህል እንደሚያኮራችሁ ስሜቱን የምትጋሩኝ ጥቂት አትሆኑም።

Thursday, October 1, 2015

ረሃብ በኢትዮጵያ በባቡር ይጋልባል (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
የኢትዮጵያ ዓመታዊ የረሃብ አዝመራ፣Famine Rides a Light Train in Ethiopia
ባለጥቁሩ ፈረስ የረሃብ የምጽዓት ቀን አስፈሪውን ፊቱን በኢትዮጵያ እንደገና ማሳየት ጀመረ፡፡
በአሁኑ ጊዜ በባቡር ተቀምጦ በመጋለብ ላይ ይገኛል፡፡
እ.ኤ.አ የካቲት 2014 በዚሁ ወር ኤንቢሲ/NBC የተባለ ዓለም አቀፍ ድርጅት ያወጣውን የምርመራ ዘገባ መሰረት በማድረግ “እየተንፏቀቀ የመጣው ረሃብ በኢትዮጵያ “ በሚል ርዕስ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ ኤንቢሲ/NBC እንዲህ የሚል ዘገባ አቅርቦ ነበር፡