Translate

Wednesday, July 30, 2014

“በኢትዮጵያዊነት ማንም ከኦሮሞዎች አይበልጥም፤ ኦርጅናል ኢትዮጵያውያን ነን” – አቶ ቡልቻ ደመቅሳ

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ለረጂም ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳትፏቸው ይታወቃሉ፤ በተለይም የኦሮሞን ህዝብ መብት እናስከብራለን ብለው የፖለቲካ ፓርቲ መስርተው ከታገሉት ሰዎች መካከል ከፊተኞቹ አንዱ ናቸው፡፡ አቶ ቡልቻ አሁን ስላሉበት የፖለቲካ ተሳትፏቸውና ስለተለያዩ አንኳር ሀገራዊ ጉዳዮች ከጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ጋር ቆይታ አድርገዋል፤ እንዲህ ይቀርባል፡-

Ato Bulcha
ነገረ ኢትዮጵያ፡- አቶ ቡልቻ በተለያዩ መድረኮች ላይ በፖለቲካ ተሳትፎዎ ነው የሚታወቁት፤ ነገር ግን አሁን ላይ ከፓርቲ ፖለቲካ ተሳትፎ የራቁ ይመስለኛል፡፡ በዚህ ወቅት ስላልዎት የፖለቲካ ተሳትፎዎ በአጭሩ ቢነግሩኝ?
አቶ ቡልቻ፡- እኔ ከመድረክ የገባሁት የኦፌኮ መሪ ሆኜ ነው፡፡ አሁን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) እስኪ ወጣቶቹ ይስሩ፣ እነሱ ሲሰሩ የሚቻለኝን እርዳታ አደርጋለሁ ብዬ በራሴ ፈቃድ ከፓርቲ ፖለቲካ ወጥቻለሁ፡፡ ‹‹Retire››  አድርጌያለሁ፡፡ እግዚአብሄር ይመስገን ጤናማ ነኝ፡፡ በእድሜየ በኩል 83 አመቴ ነው፡፡ በትምህርትም ሆነ በተፈጥሮ ስጦታ ትልቅ አቅም ያላቸው ልጆች ስላሉ እኔ በዚህ እድሜዬ መድከም የለብኝም ብዬ ነው የለቀቅኩት፡፡

ኦሮሞ እና እስልምና በ“ሕዳሴ አብዮት” መስመር (ተመስገን ደሳለኝ)

ኦሮሞ እና እስልምና በ“ሕዳሴ አብዮት” መስመር (ተመስገን ደሳለኝ)

በወርሃ-ግንቦት ላይ ለዘመናት የተንሰራፋውን ሀገራዊ ደዌ ይፈውሳል ብዬ ተስፋ ስለማደርግበት “የሕዳሴ አብዮት” በሶስት ተከታታይ ክፍሎች ለመዳሰስ መሞከሬ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ መጪው የ “ሕዳሴ አብዮታችን” መፍትሔ ሊሰጥባቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መሀል በዋነኝነት የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪው ማሕበረሰብ እና የእስልምና እምነት ተከታዮች የመብት ጥያቄን በተመለከተ በጥቅሉ ጠቃቅሼው አልፌ ነበር፡፡ ሆኖም ‘ሰፋ ብሎ ቢዳሰስ’ የሚሉ በተለያየ መንገድ የሚቀርቡ ጎትጓች ድምፆች መበራከታቸው የመነሻ ሃሳቡን ፈታ አድርጌ እንዳቀርብ አስገድዶኛል፤ እንግዲህ ይህ ጭብጥም የዛው ተከታይ መሆኑ ይሰመርልኝ፡፡

Monday, July 28, 2014

ሳውዲ የሚገኙት በረከት ስምዖን ጤና እያነጋገር ነው


bereket_simon

እሁድ ከአዲስ አበባ አንድ የጦር ሃይሎች ሆስፒታል ዶ/ር አስከትለው በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕላን እኩለ ሌሊት ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ለህክምና በድብቅ እንደገቡ የሚነገርላቸው አቶ በረከት ስሞኦን በተለምዶ ብግሻን እየተባለ የሚጠራ አንድ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ የልብ ደም ቧንቧ ለማስፋት ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ከሳውዲ አየር መንገድ ምንጮቻችን ለማረጋገጥ ተችሏል። የበረከት ጤንነት በአሁኑ ሰዓት በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት እነዚህ ምንጮች ዛሬ ጠዋት ከመካ የዒድ አል ፈጠር የፀሎት ስርዓት በኋላ ሼክ አላሙዲን በስልክ እንዳነጋገሯቸው ይናገራሉ።

ፖሊቲካና የግለሰብ ጠባይ

(ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

two

ለእኔ ፖሊቲካና የግለሰብ ጠባይ እንደውሃና ዘይት የማይደባለቁ ነገሮች ይመስሉኛል፤ አጼ ምኒልክ ‹‹አመልህን በጉያህ›› ያሉት ለዚህ ሳይሆን አይቀርም፤ ዘይትና ውሀ በባሕርያቸው የሚለዩትን ያህል ፖሊቲካና ግለሰብም የባሕርይ ልዩነት አላቸው ማለት ነው፤ የወያኔ መሪዎች ምንም ነገር የማይሰምርላቸው፣ ከመጀመሪያውኑ እነዚህን ሁለት የማይደባለቁ ባሕርዮች አደባልቀው በመንሣታቸው ነው፤ ፖሊቲካ ለማኅበረሰቡ መቆርቆር ነው፤ ለሕዝቡ መቆርቆር ነው፤ ለአገር መቆርቆር ነው፤ የፖሊቲካ መነሻም ይኸው መሆን አለበት፤ ዓላማውም የማኅበረሰቡ፣ የሕዝቡ ልማት እንጂ ጥፋት አይደለም፤ የነበረውንና ያለውን ማጥፋት የፖሊቲካ ዓላማ ሊሆን አይችልም።

በስቃይ ላይ ተመርኩዘው የሚወጡ ቃላቶች የአንዳርጋቸው እንዳልሆኑ መናገር ይቻላል።

በስቃይ ላይ ተመርኩዘው የሚወጡ ቃላቶች የአንዳርጋቸው እንዳልሆኑ መናገር ይቻላል።

አባይ ሚዲያ፡ እንደተለመደው ሁሉ ወያኔዎች የኢትዮጵያ ህዝብ እንደማያምናቸው በተረዱ ጊዜ በርካታ ዘዴዎችን እየፈጠሩ ማሀበረሰቡን እያዋረዱ ረግጠው ለመግዛት ያላቸውን ሃይል ሁሉ ተጠቅመው ለማሳመን ጥረት ማድረጋቸውን እያየን ነው። ይህም አንዳርጋቸው እኔ ደህና ነኝ በል ተብሎ ያለው እና “እንደምታዩት ነው” ያለው ትልቅ መልእክት አለው።

Sunday, July 27, 2014

ሰማያዊ ፓርቲ ያዘጋጀውን የዜጎች ቃል-ኪዳን ሰነድ (ሕገ መሰረት) ለህዝብ ይፋ አደረገ


የዜጎች ቃል-ኪዳን ሰነድ ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ
ክፍል ፩
መግቢያ
ይህ የዜግነት ቻርተር (ቃል-ኪዳን እና ሕገ-መሠረት) ከፖለቲካዊ አድናቂነት ነጻ የሆነ፤ ሁሉን-አቀፍ ምሰሶ የሆኑ መርህዎችን ያካተተ የማሕበረሰብ (የሲቪክ) ንቅናቄ ሰነድ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከየት ወደ የት ለሚለው አንገብጋቢ ጥያቄም መሰረታዊ መልስን ያቀፈ ራዕይን የሚያስተጋባ የኩሩ ዜጎች መለያ ነው፡፡ ይህም ማለት፡-

ኢትዮጵያ በፍርሀት የሞት እና ሽረት ትግል መካከል የምትንጠራወዝ ምስኪን አገር፣

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
(የጸሐፊው ማስታወሻ) በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ገዥ አካል  በቅርቡ ገንቢ ያልሆነእና በእራስ አሸናፊነት ጎልቶ ለመውጣት በሚል ዕኩይ ምግባር በተቃዋሚዎቹ እናትችት በሚያቀርቡበት ወገኖች ላይ እየወሰደ ያለውን የቅጣት እርምጃ አሳፋሪ ነው::ገዥው አካል በተደጋጋሚ በሚሰራቸው አስቂኝ የስህተት ቀልዶች (በሚከተላቸውብልሽቶች እና ድሁር አቅመቢስነትእና በሚፈጽማቸው የመድረክ ትወናዎች(ለአጭር ጊዜ እኩይ ፍላጎቱ እርካታ ሲል በሚያራምዳቸው ውዥንብሮቹበሁለቱምድርጊቶቹ የሚያስደንቅ እና ግራ የሚያጋባ ሆኗል ፡፡ ገዥው አካል ለምንድን ነው 20እና ከዚያ በላይ የሚሆኑ ጦማሪያንን እና በጣት የሚቆጠሩ ሃያሲ ጋዜጠኞችን ሸፍጥበተመላበት ሁኔታ በሀሰት በተፈበረከ እራሱ “አሸባሪነት” እያለ በሚጠራው ክስ ከሶበእስር ቤት አጉሮ ንጹሀን ዜጎችን እያማቀቀ ያለውለምንስ ነው ክቡር የሆነውንየጋዜጠኝነትን ሙያ እየወነጀሉት ያለውለምንድን ነው ገዥው አካል የአገሪቱንኢኮኖሚ በመዳፉ ስር ጨምድዶ ይዞ  በተጠንቀቅ በአንድ ቦታ ቆሞ የሚጠባበቅወታደራዊ ኃይል እያለው እና ብዛት ያላቸው ጠብመንጃዎች፣ ታንኮች እና የጦርአውሮፕላኖች በእራሱ ቁጥጥር ስር እያሉት በጥቂት ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ልቡበፍርኃት እየራደ በጭንቀት ማዕበል ውስጥ እየዋኘ የሚገኘውጉልበትን እንጅ ህግንእና ስርዓትን የሚጠየፈው ገዥ አካል በነጋ በጠባ ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ በመፎከር የራሱ ጥላ አያስበረገገው ተሸበሮ የሚሸበረው? 

Friday, July 25, 2014

ለብሔራዊ አንድነትና ነፃነት – ህወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መነጠል!!!

ለብሔራዊ አንድነትና ነፃነት – ህወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መነጠል!!!

Untitled g7
በአለፉት ጥቂት ሣምንታት በወያኔ የተፈፀሙ የእብደት ተግባራትን ስናጤን ከፊት ለፊት ኢትዮጵያችንን እየጠበቀ ያለው መንታ መንገድ አመላካች ነው። ይህ ከፊት ለፊት የሚጠብቀን መንታ መንገድ አንዱ ወደ ብሔራዊ አንድነት፣ ነፃነትና ብልጽግና ሌላው ወደ እርስ በርስ ትርምስና ውድቀት የሚያመሩ ናቸው። የአንድነት፣ የነፃነትና የብልጽግና መንገድ ለመያዝ መስመራችንን ማስተካከል ያለብን ከአሁኑ ነው።
ለመሆኑ ከላይ ያልነውን ለማለት ያስቻሉን በአለፉት ጥቂት ሣምንታት በወያኔ የተፈፀሙት ተግባራት ምንድናቸው?
አንደኛ፤ ወያኔ፣ ዓለም ዓቀፍ ህግንና ሥርዓትን በጣሰ መንገድ ከየመን ባለሥልጣናት ጋር በማበር የንቅናቄዓችንን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ማፈኑ በአለፉት ጥቂት ሣምንታት ውስጥ ውስጥ የተደረገ አብይ ክስተት ነው። ይህ የወያኔ የውንብድና ተግባር ኢትዮጵያዊያንን በእጅጉ አስቆጥቷል። ወያኔ፣ ለሀገር ነፃነትና ለእኩልነት የሚታገልን አንድ ታላቅ ሰውን ማፈንኑና ከእይታ ከልሎ እያሰቃየው መሆኑ በሕዝቡ ውስጥ ያለው ቁጣ ወደ መገንፈል አስጠግቶታል። አቶ አንዳርጋቸው በጠላት እጅ ከወደቀም በኋላ ኢትዮጵያዊያንን አሰባሳቢ ኃይል ሆኗል።

Monday, July 21, 2014

ቀጭኗ፤ ፖለቲከኛ ሀሙስ ፍርድ ቤት ትቀርባለች፤ እና ሌሎች ቀጫጭን መረጃዎች

983744_10152978488915830_7057766400299394261_nAbe Tokchaw
ወይንሸት ሞላ የሰማያዊ ፓርቲ አባል እና የወጣቶች ጉዳይ ውስጥ አመራር ላይ ካሉት ሃላፊዎች አንዷ ነች። ጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ ሲገልጻት ”ቀጭን እና ጠንካራ” ይላታል። ይቺ ልጅ አርብ እለት (ጁምዓ) በአንዋር መስጊድ ሙስሊም ወንድሞች እና እህቶቻችን ሰላማዊ ጸሎት ለአላህ፤ እና ሰላማዊ ተቃውሞ ለመንግስት በሚያሰሙ ጊዜ የመንግስት ታጣቂዎች ያገኙትን መደብደብ እና ማፈስ ሲጀመሩ ወይ ጉዳዩን ለመታዘብ ስትበር በቦታው ተገኝታ፤ አልያም በአጋጣሚ በአንዋር መስጊድ አካባቢ ስታልፍ ብቻ ለጊዜው ለዚህ ዜና ጸሀፊ ግልጽ ባልሆነ አጋጣሚ አንዋር መስጊድ አካባቢ ከዚህ በፊት ይከታተላት የነበረ ደህነነት አያት፤ ከዛም ለቀም አድርጎ እየደበደበ ከፖሊሶች ጋር ተባብሮ ወሰዳት። ከዛም ማንም የርሷ ወገን ባልተገኘበት ፍርድ ቤት አቀረቧት፤ ይቺ ቀጭን ወጣት እና ጠንካራ ፖለቲከኛ ዳግም ለሐሙስ ሐምሌ 16 ሜክሲኮ አካባቢ በሚገኝ ፍርድ ቤት ትቀርባለች።
10526174_10202973686676502_6338511177552984735_nሌላ የፎቶ ጋዜጠኛ የሆነችው አዚዛ መሃመድ የፎቶ ካሜራ ለአዲስ ጉዳይ መጽሄት ዘገባ በአንዋር መስጊድ ባለፈው አርብ የተፈጸመውን ድርጊት በካሜራዋ ስታነሳ በመገኘቷ የመንግስት አሳሪዎች አስርዋታል። አዚዛም ማንም በሌለበት ፍርድ ቤት የቀረበች ሲሆን አሁንም ሀሙስ ሃምሌ አስራ ሰባት በቂርቆስ ከፈለከተማ ምድብ ችሎት ከሌሎች በርካታ ታፍሰው የተወሰዱ ንጹሃን ጋር ዳግም ፍርድ ቤት ልትቀርብ ቀጠሮ ተይዞላታል።

’’የነብርን ጂራት አይዙም ከያዙም አይለቁም’’!

’’የነብርን ጂራት አይዙም ከያዙም አይለቁም’’!

ከአየነው ብርሃኑ

የኢትዮጵያ ህዝብ አዋቂ ነው ታጋሺም ነው። ቸኮሎ ለዉሳኔ አይነሳም የፊቱን የኋላዉን የቀኙንም ሆነ የግራዉን የማየት ነገሮችንም የማመዛዘን ብቃቱ አለዉ።
ለዚህም ነው እነዚህ ጥቂት የዘር ልክፍት የተጠናዎታቸዉ ጥቂት የትግሬ ዘረኞች በዘር መከፋፈል የዘላለም ገዢንታችንን ያረጋግጥልናል በሚል ከንቱ  ተስፋ  በኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ የዘመቱት።
እኛ እየናቅናቸዉ እነሱ እየፈሩን ይኸዉ ሩብ ዓመት ሞላቸዉ።የፈሪ በትራቸዉን ያለ ርህራሄ ኣሳረፉብን አሳደዱን ፤ ሲፈልጉ በመርዝ ስያጠፉን ፤እንዲያም ሲል በአደባባይ ሲረሽኑን ይኸው ድፍን ሩብ ምዕተ ዓመት ሊሞላ ነው።

Sunday, July 20, 2014

ነጻነትን ለመጎናጸፍ ባሩዷን ማሽተት የግድ ነው !!! ሪያድ ኢብራሂም

ነጻነትን ለመጎናጸፍ ባሩዷን ማሽተት የግድ ነው !!!
የወያኔ የግፍ ስርዓት በህዝብ ትከሻ ላይ ድሩን አድርቶ ፤ የማይጠረግ እስኪመስለን ድረስ ሁለት አስርት አመታቶችን በላያችን ላይ ዘልቋል ።በሰላማዊ መንገድ የግፉ ስርዓት ተቋጭቶ ፍትህና እኩልነት በሀገራችን ይሰፍን ዘንድ ብዙ ተሞክሯል ። ነገር ግን በወያኔ ስልጣን አልጠግብ ባይነት እና የሰላማዊው መንገድ ክርችም ብሎ በመዘጋቱ ባሩዷን ማሽተት ግድ የሆነበት ጊዜ ላይ ከደረስን ከራርመናል ።ትግሉ ከኛ ምን ያህል የአላማ ጽናትን ይፈልጋል ? ምን ያህልስ መስዋእትነትን ያስከፍለናል ? እንዴትስ ብንታገል ካሰብነው የነጻነት ደጃፍ ባጭሩ ያደርሰናል ብለን ብንጠያየቅ ትክክለኛ ጊዜው አሁን ይመስለኛል።

አቶ አንዳርጋቸው ታፍኖ የተወሰደበት ቦታ እስከአሁን አልታወቀም ነገር ግን በደህንነት ሰዎች በደረሰበት ድብደባ ራሱን በመሳቱ ለህክምና ከአዲስ አበባ ውጪ ይዘውት ወጠዋል የሚሉ አስተያየቶች እየተበራከቱ ነው።

አቶ አንዳርጋቸው ታፍኖ የተወሰደበት ቦታ እስከአሁን አልታወቀም ነገር ግን በደህንነት ሰዎች በደረሰበት ድብደባ ራሱን በመሳቱ ለህክምና ከአዲስ አበባ ውጪ ይዘውት ወጠዋል የሚሉ አስተያየቶች እየተበራከቱ ነው።
ዛሬ የአዲስ አበባ ምንጫችን ብዙ ቦታዎችን ለማካለል ሞክሬ ነበር ነገር ግን የአንዳርጋቸው ይኖርበታል ተብሎ የሚገመቱ ቦታዎችን ማግኘት እንዳልቻለ ይሁን እንጂ ከደህነነት ሰዎች አንዱ በሆነ መኖሪያ ቤት ውስጥ ሊኖርም እንደሚችል የግል አስተያየቱን ልኮልናል።
ዘጋቢያችን አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በማናገር አቶ አንዳርጋቸው በአሁኑ ሰአት ከሰውነት ክፍሉ ውስጥ አንዱን ሰብረዉት ወይም ቆርጠውት እንደሚሆን  ስቃዩን በማብዛት ነገር ግን  እንዳይሞትባቸው ከአዲስ አበባ ውጪ ለህክምና ይዘውት ወጥተው ይሆናል የሚል በርካታ አስተያየቶች  መሰብሰቡን ዘግቦል።

Friday, July 18, 2014

ጁምዓ በፖሊስ ጥቁር ሽብር ተናወጠ

ኢ.ኤም.ኤፍ) ዛሬ አርብ ጁምዓ ነበር። የረመዳን ጾም እንደመሆኑ መጠን፤ ለስግደት በጣም ብዙ ሺህ ህዝብ ወደ ታላቁ አንዋር መስጊድ ሄዷል። ከኢህአዴግ ጋር ተመሳጥረው ሙስሊም ወንድሞቻቸውን አሳልፈው በሰጡ እና የ”ኮሚቴ አባሎች” ይፈቱ በሚሉ ሰላማዊ ሙስሊሞች መካከል የተፈጠረው ውጥረት አሁንም እንዳለ ነው። ኢህአዴግ መራሹ መንግስትም ይህን የመከፋፈል አጋጣሚ በመጠቀም፤ “ድምጻችን ይሰማ” የሚሉ ወገኖችን በመደብደብ እና በማሰር መፍትሄ ለማግኘት የሚያደርገውን ጥረት ቀጥሏል።
addis police5
ሹመኛ የመጅሊስ አመራሮችን ዛሬ በይፋ ህዝብ አውርዷቸዋል!!
ይህ አይነቱ በጨለምተኝነት ላይ የተመሰረተ የኢህአዴግ ድርጊት፤ በህዝብ ላይ የሚተገበር “ጥቁር ሽብር” ከማለት ውጪ ሌላ ትርጉም የሚሰጠው አይደለም። ለዚህም ነው በርእሳችን ላይ “ጁምዓ በፖሊስ ጥቁር ሽብር ተናወጠ” ያልነው።  ይህ ሽብር እና ነውጥ ምን ይመስል እንደነበር የበለጠ ለመረዳት በስፍራው ተገኝተው፤ የአይን ምስክር ሆነው ዘገባቸውን ያቀረቡትን የጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና የጌታቸው ሽፈራውን ዜና መመልከት በቂ ነው። በቅድሚያ ጋዜጠኛ ኤልያስን ዘገባ እናስቀድማለን።

Thursday, July 17, 2014

አገራዊ ጥሪ ለመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት

ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የኢትዮጵያ የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላትን ከአለቆቻቸው ለይቶ ይመለከታል።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት ከፍተኛ ሹማምንት ከህወሓት የተቀዱ፣ ለህወሓት ሥልጣን የቆሙ፣ ዘረኞች፣ ፋሽስቶችና ሙሰኖች መሆናቸው በገሃድ የሚታወቅና በተደጋጋሚ ጥናቶችም የተረጋገጠ ጉዳይ ነው። በዘመነ ወያኔ የሠራዊት አዛዥነት ሹመት መሥፈርቶች ዘር፣ የፓለቲካ አመለካከትና ለህወሓት ያላቸው ታማኝነት ነው። በዚህም ምክንያት ሁሉም ቁልፍ የአዛዥነት ቦታዎች የተያዙት ሙሉ በሙሉ የህወሓት አባላት በሆኑ የትግራይ ተወላጆች ነው። እነዚህ የጦርና የፓሊስ ሹማምንት ኢትዮጵያን ወረው እንደያዙት አገር ሲዘርፉ፣ ሕዝቧንም ሲገሉና ሲገርፉ እንሆ 23 ዓመታት አልፈዋል። በእነዚህ 23 ዓመታት ትግራይን ጨምሮ በደል ያልደረሰበት የኢትዮጵያ ግዛት እና የኅብረተሰብ ክፍል የለም። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በእነዚህ ፋሽስቶች ተረግጧል፣ ተዋርዷል፣ ተግዟል። የንቅናቄዓችን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የነፃነት አርበኞች በእነዚህ እኩይ የሠራዊቱና የፓሊስ አዛዦች ሰቆቃ እየተፈፀመባቸው ነው። የወያኔ የጦርና የፓሊስ አዛዦች እና ሰላዮች አገራችን እያደሙ፤ ሕዝባችንን እያስለቀሱ ነው። በወያኔ ፋሽስት የጦርና የፓሊስ አዛዦች እና ሰላዮች ጥምረት ሰቆቃ የሚፈፀምበት የኅብረተሰብ ክፍል በየጊዜው እየጨመረ ይገኛል። የወያኔ ማሰቃያዎችን የሞሉት የፓለቲካና የሀይማኖት መሪዎች፣ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች መሆናቸው ለዚህ አንድ ማሳያ ነው።
የሠራዊቱ የበታች ሹማምንትና ተራ አባላት ጥንቅር ግን ከአዛዦቹ ፈጽም የተለየ ነው። የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ከመላው የኢትዮጵያ ግዛቶች የተውጣጡ፤ እንደሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ በነፃነት እጦት፣ በመብቶች መገፈፍ እና በኑሮ ውድነት የሚሰቃዩ ዜጎች ናቸው።

ጠበቆቻቸው በሌሉበት በጋዜጠኞች እና ጦማሪዎች ላይ የሽብር ክስ ተመሰረተ

(ኢ.ኤም.ኤፍ) ከቤታቸው እና ከያሉበት ቦታ ታፍነው ከተወሰዱ ሶስት ወራት ያስቆጠሩት ዘጠኝ ጋዜጠኞች እና ጦማሪዎች ላይ፤ አቃቤ ህግ በሽብርተኝነት ወንጀል እንዲቀጡ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው የአቤቱታ ሰነድ አመልክቷል።ፖሊስ ዘጠኙን ይዞ የቀረበው ያለምንም ማስጠንቀቂያ እና ቀጠሮ በመሆኑ ቤተሰብም ሆነ፤ ጠበቆቻቸው በስፍራው አልተገኙም ነበር። ሆኖም አቃቤ ህጉ ፖሊስ ባቀረባቸው ዘጠኝ ወጣቶች ላይ የክስ መዝገብ አስከፍቶ የክስ ቻርጁን ሰጥቷቸዋል።
እንደ ክስ ቻርጁ ከሆነ አቃቤ ህግ ሽብርተኛ ያላቸው ጦማሪያን፣ ሶልያና ሽመልስ (በሌለችበት ነው የተከሰሰችው)፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ አጥናፉ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አቤል ዋበላ፣  ዘለዓለም ክብረት፣  ሲሆኑ ከነሱ ጋር ጋዜጠኞቹን አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬና ተስፋለም ወልደየስ በተመሣሳይ ሁኔታ በአሸባሪነት እንዲቀጡለት መጠየቁን የኢ.ኤም.ኤፍ ዜና አቀባይ ገልጾልናል –  ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2006 ዓ.ም. (ጁላይ 17፣ 2014)፡፡
የአሸባሪነት ክስ የተመሰረተባቸው ጋዜጠኞች እና ጦማርያን።
የአሸባሪነት ክስ የተመሰረተባቸው የዞን9 – ዘጠኝ ጋዜጠኞች እና ጦማርያን።
የኢ.ኤም.ኤፍ ዜና አቀባይ እንደገለጸው ከሆነ ፖሊስ ልደታ በሚገኘው ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በድንገት ይዟቸው በመቅረቡ ምክንያት ጠበቆቻቸው በስፍራው አልነበሩም።፡ በመሆኑም “ጥፋተኛ ነኝ ወይም አይደለሁም” ለማለት ጠበቆቻቸው በተገኙበት መፈጸም ስላለበት፤ በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር ነገ ከጠዋቱ 3 ሰአት ላይ እንደገና እንዲቀርቡ ተብሏል።
የሆኖ ሆኖ አቃቤ ህጉ አቅርቦት የነበረው ወይም በክስ ዝርዝሩ ላይ “ወጣቶቹ ከአሸባሪዎቹ ግንቦት ሰባት እና ኦነግ ጋር በመመሳጠር መንግስት ለመጣል ሙከራ አድርገዋል” ብሏል። ከነሱም መካከል በሌለችበት ክስ የተመሰረተባት ሶሊያና ካለፉት ሁለት አመታት ጀምሮ ጦማርያኑን በማስተባበር እና የውጭ ጉዳይ ሃላፊ በመሆን ሰርታለች የሚል ክስ አቅርበውባታል።

ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ ፍ/ቤት ሳይቀርቡ የምርመራ መዝገቡ መዘጋቱ ሕገወጥና አደገኛ መሆኑ ተገለጸ

"አሁን ታስረው የሚገኙበት ሁኔታ ሕገወጥና አደገኛ ነው" ጠበቃ አመሐ መኮንን

zone9 free


በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በክስ ላይ የሚገኙት ሦስት ጋዜጠኞችና ስድስት ጦማርያን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ፖሊስ ‹‹ምርመራዬን ስለጨረስኩ መዝገቡ ይዘጋልኝ›› በማለት መዝገቡ እንዲዘጋ ማድረጉ ሕጉን ያልተከተለና አደገኛ መሆኑን ጠበቃቸው አስታወቁ፡፡

Wednesday, July 16, 2014

ሚሚ ስብሐቱ እና የሙታን ዲሞክራሲ (በዶ/ር ዳኛቸው)


የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ሚሚ ስብሐቱና ጓደኞቿ “የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ” በተሰኘ ፕሮግራም እኔ ላይ ለሰነዘሩት ስድብ በዋናነት መልስ ለመስጠት ሳይሆን ዘለፋቸውን በሚካሄዱበት ሰዓት እግረ መንገዳችውን ባነሱት የፖለቲካ አተያይ ላይ ሒስ ለማቅረብ ነው፡፡ይህንንም እንድል ያስገደደኝ እኔ ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ተደውሎ ለቀረበልኝ ጥያቄ በሰጠሁት መልስ ላይ ወይም ባነሳሁት ሐሳብ ላይ ትችት በማቅረብ ፈንታ በእኔ ስብዕና ላይ አሉታዊ በሆነ መልኩ ዘለፋ በመሰንዘራቸው ነው፡፡

Tuesday, July 15, 2014

ጥላቻ በዛ፣ ቂም አበበ፣ በቀል አፈራ!! ኢህአዴግም አልረካም

የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉዞ አስቀድሞ እንዴት ታወቀ?

prisoners1


“እነሱ ሁለት አገር አላቸው። ኢትዮጵያን ይዘዋታል። በስደትም እንደፈለጋቸው እየኖሩ ነው። እኛ ግን አንድም አገር የለንም። በስደት እንኳን እንዳንኖር እየተደረግን ነው። ሸሽተን በተሰደድንበት ምድር እንኳን ዋስትና የለንም። ከዚህ በላይ ምን ይምጣ?” ይህንን የዛሬ ሶስት ወር ገደማ ለጎልጉል የተናገሩት በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር ጸሐፊ ወ/ት የሺሃረግ በቀለ ነበሩ። የወ/ት የሺሃረግን ሃሳብ በመንተራስ ለጎልጉል አስተያየት የሰጡ እንዳሉት “አገር ውስጥም እስር፣ በስድት ምድርም ስጋትና እስር ካለ፣ የይለይለት መንፈስ መነሳቱ አይቀርም።

የዘር ማጥፋት ወንጀሎች በአማራ ሕዝብ ላይ በታሪክ ሂደት ውስጥ ከጥንት እስከ ዛሬ!

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

displaced

ይሄንን ጽሑፍ ታች አምና ከጉራፈርዳና አካባቢው አማራ በመሆናቸው ምክንያት ብቻ ሕጋዊነታቸውን የሚያረጋግጡ ሰነዶችን ይዘው እያለ ሕጋዊ ሆነው የየክልሉ መንግሥት አውቋቸው በሥርዓቱ ግብር እየከፈሉ እየኖሩ የነበሩ ምስኪን ገበሬዎችን “ሕገ ወጥ ሰፋሪዎች”  በሚል ሕገ ወጥነታቸው አግባብነት ባለው የሕግ አካል (ፍርድቤት) ክስ ተመስርቶባቸው ሳይረጋገጥባቸው በጅምላ በግፍና በሕገ ወጥ መንገድ ንብረታቸውን ሁሉ ተወርሰው እንዲወጡ በተደረገ ጊዜ ጽፌው ለጥቂት መደበኛና ኢመደበኛ (Conventional and Social Media) ልኬው ነበር እስከማውቀው ድረስ ለሕዝብ ይፋ አድርገውት ያስነበቡት ወይም ያስደመጡት አልነበሩምና ሕዝብ ሊያውቃቸው የሚገባ በርካታ ቁምነገሮች ስላሉት እንዳያመልጣቹህ በማሰብ ወደ እናንተ አድርሸዋለሁ መልካም ንባብ፡፡

አኖሌ ሃውልት ፖለቲከኞችና የታሪክ ምሁራንን እያወዛገበ ነው


politicians and scholars


በምኒልክ ዘመን በኦሮሞ ተወላጆች ላይ ተፈፅሟል የተባለውን የጡትና እጅ መቁረጥ ኢ-ሰብአዊ ድርጊትና ጭፍጨፋ ለማስታወስ በሚል በአርሲ አኖሌ አካባቢ በ20 ሚሊዮን ብር የተሰራው ሃውልት፣ በቅርቡ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሙክታር ከድርን ጨምሮ በርካታ የኦህዴድ ባለስልጣናት በተገኙበት ተመርቋል፡፡
ሃውልቱን ያሰራው አካል ያለፈን ታሪክ መዞ ቂም በቀልን ለማውረስ ሳይሆን ቀጣዩ ትውልድ ከአስከፊው ድርጊት እንዲማርና ወደፊት ድርጊቱ እንዳይደገም ነው ሃውልቱ የተገነባው ብሏል፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና ምሁራን በበኩላቸው ለሁለት ተከፍለዋል፡፡ አንደኛው ወገን  ሃውልቱ በህዝቦች መካከል ቅራኔና ቂም በቀል የሚፈጥር ነው በማለት ሲቃወም ሌላው ወገን በበኩሉ ድርጊቱ ዳግመኛ እንዳይከሰት መማርያ እንጂ የበቀል አይደለም ሲሉ የሃውልቱን መቆም ይደግፋሉ፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ፣ አወዛጋቢ በሆነው የአኖሌ ሃውልት ዙሪያ የታሪክ ምሁራንንና ፖለቲከኞችን አነጋግሮ እንደሚከተለው አጠናቅሮታል፡፡

Monday, July 14, 2014

ሰበር ዜና - የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከእንግሊዝ ለኢትዮጵያ ዕርዳታ የሚሰጡ ድርጅቶች በሙሉ (የእንግሊዝ መንግሥትንም ጨምሮ) ለኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ቅድምያ መስጠታቸውን እና አለመስጠታቸውን በሚያጣራ መልኩ ሕጋዊ ምርመራ እንዲደረግ አዘዘ


ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት (ሁማን ራይት) ዛሬ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ባሰራጨው ዜና  የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከእንግሊዝ ለኢትዮጵያ  ዕርዳታ የሚሰጡ ድርጅቶች በሙሉ (የእንግሊዝ መንግሥትንም ጨምሮ) ለኢትዮጵያ የሰብዓዊ  መብት ይዞታ ቅድምያ መስጠታቸውን እና አለመስጠታቸውን በሚያጣራ መልኩ ሕጋዊ ምርመራ እንዲደረግ ያሳለፈውን ውሳኔ  ''ጠቃሚ እርምጃ'' በማለት አሞካሽቶታል።
ውሳኔው በተለይ በቅርቡ ከአርበኛ አንዳርጋቸው ፅጌ መታገት በኃላ የእንግሊዝ መንግስት  ''የባህር ማዶ የልማት ትብብር ድርጅት'' (UK Department for International Development (DFID) ) ለኢትዮጵያ መንግስት የገንዘብ ድጎማ ሊያደርግ የነበረ ከመሆኑ አንፃር የዛሬው ውሳኔ ከፍተኛ መልዕክት ማስተላለፉ አይቀርም።በሌላ በኩል የዛሬው የፍርድቤቱ ውሳኔ ይሄው የልማት ድርጅት (DFID) በበቂ ሁኔታ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ ይዞታ ጉዳይ አለመመርመሩን ጠቁሞ በእዚሁ አዲሱ የፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት ሕጋዊ ምርመራ እንዲደረግበት ማዘዙን ያብራራል።

አዋጅ አዋጅ !!!……….. ልብ ያለዉ ልብ ይበል ጆሮ ያለዉ ይስማ !!

አዋጅ አዋጅ !!!……….. ልብ ያለዉ ልብ ይበል ጆሮ ያለዉ ይስማ !!
የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል የተሰጠ መግለጫ
አዋጅ አዋጅ !!!
ልብ ያለህ ልብ በል ጆሮ ያለህ ስማ !!
የግንቦት7 ህዝባዊ ሃይል የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በየመን መታገት አስመልክቶ አጭር መግለጫ ማውጣቱ ይታወቃል።በመግለጫችን የመን ታጋዩን ልታግት የምትችልበት የጸጉር ስንጣቂ የምታክል ምክንያት እንደሌላት ሊኖራትም እንደማይችል ስለሆነም ታጋዩ ባስቸኳይ እንዲለቀቅ በተደጋጋሚ ጠይቀን፣ ይህ ሳይሆን ቀርቶ የነጻነት ታጋዩ ለፋሽስቱ የወያኔ ቡድን ተላልፎ ቢሰጥ የመን የማይሰረዝ ታሪካዊ ስህተት የምትሰራ መሆኑን ህዝባዊ ሃይላችንም የበቀል እርምጃዎችን እንደሚወስድ አሳውቀን ወያኔም ምናልባት ትግሉን አስቆማለሁ በሚል የሞኝ ስሌት ያደረገው ከሆነ ድርጊቱ ትግሉን በዕልህ እና በበቀል አጅቦ ከመውሰድ እና ከማፋጠን የዘለለ ትልቁ የሃሳብ አባት አንዳርጋቸው በሃገሪቱ ሰማይ ላይ የለቀቀውን የኢትዮጵያዊነት ጸረ ወያኔ መንፈስ አስሮ አሰቃይቶ፣ገሎ ማስቆም እንደማይችል አሳስበን አስገንዝበን ነበር። መግለጫችን የተጻፈበት ቀለም ሳይደርቅ ግን የየመን መንግስት እንደሰጋነው ትልቁን የቁርጥ ቀን ልጅ ለወያኔ አሳልፎ መስጠቱን አውቀናል።

ጥቂት ነጥቦች በፍትህ ጉዳይ ላይ ታደሰ ብሩ

1. መግቢያ
ህወሓት በሥልጣን ላይ በከረመ መጠን የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍትህ እጦት የሚደርስበት መከራ እየጨመረና እየመረረ በመምጣቱ “ፍትህ አጣን፤ የፍትህ ያለህ” የሚሉ እሮሮዎች ከቀድሞው በበለጠ መልኩ እየጎሉ መጥተዋል። በከተማውም በገጠሩም፣ ከእድሜ ባለፀጋውም ከወጣቱም፣ ከወንዱም ከሴቱ፣ ከክርስቲያኑም ከሙስሊሙም ወገኖቻችን የሚሰማው ጩከት “የፍትህ ያለህ” የሚል ነው። የፍትህ እጦት ነው ወገኖቻችንን በገዛ አገራቸው ተፈናቃይ ያደረጋቸው፤ የፍትህ እጦት ነው ገበሬዎች ማሳቸው ለባዕዳን ሲሰጥ አንጀታቸው እያረረ ዝም እንዲሉ የሚያደርጋቸው፤ የፍትህ እጦት ነው ነጋዴዎች ሱቆቻቸው በእሳት ሲጋዩ “ጉዳዩ ይጣራልን” ማለት እንኳን ያላስቻላቸው፤ የፍትህ እጦት ነው የእምነት ነፃነታችንን እንኳን ማስከበር ያላስቻለን።

የሕወኀትን ዕቅዶች እንዴት ማክሸፍ ይቻላል?

ለሕወኀት ቀኑ በፍጥነት እየጨለመ መሆኑ ግልጽ ቢሆንም እስካሁንም ምንም ዓይነት የማስተካከያ ርምጃም ሆነ የመለሳለስ አቋም ከማሳየት ይልቅ በተለመደው እብሪቱ የመቀጠሉ ምክንያት ሊሠራ የሚችል ዕቅድ አለኝ ብሎ ከማመን ነው። ከሰሞኑ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ከየመን አግቶ እስከመውሰድ ድረስ የደፈረበት ድርጊት አገዛዙ የደረሰበትን የፍርኃት ደረጃ በግልጽ የሚያሳይ ቢሆንም ‘መውጫ ቀዳዳ አለኝ’ ብሎ የሚያስበው አስተሳሰብ ሥር የሰደደ መሆኑን የሚያመለክትም ጭምር ነው። ‘እነዚህን ዕቅዶች ብዙ ሠርቸባቸዋለሁ፣ ዝግጅቶቸን ወደማጠናቀቅ ደርሻለሁ፣ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር እየኖሩ ከመሥጋት እጅግ የተሻለ ዕቅድ ነው’ ብሎ ያምናል። ይህ ለሌሎችም እንዲተባበሩ ለሚጠየቁት/ ለሚገደዱት ቢያንስ ለሁለቱ ክልሎች (የቤንሻንጉል ጉሙዝና ጋምቤላ) እንደምክንያት የሚቀርብ ሐሳብ እንደሚሆን መገመት ይቻላል። ይሁን እንጂ ዕቅዱን ለማክሸፍ የሚቻልባቸው አያሌ መንገዶች አሉ። የሚከተሉት ጥቂቶቹ ናቸው። ሌሎች ቢጨምሩባቸውና ቢያዳብሯቸው ጥቅሙ ለሀገርና ለወገን ነው።

Sunday, July 13, 2014

የየመን አወዛጋቢ አሳልፎ የመስጠት ውሳኔ ና የእንግሊዝ አቋም

ዜናው የአቶ አንዳርጋቸውን ንግግር ለአፍታ ያቀረበ ሲሆን ይዘቱ ግን ግራ ያጋባቸው በርካቶች ናቸው፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ‹‹እኔ አሁን ከራሴ ጋር ታርቄ ሰላም አግኝቻለሁ፡፡ እውነቴን ነው የምልህ እኔ እንደ ምርቃት ነው የተቀበልኩት፡፡ አሁን የሚያስቸኩለኝ ነገር የለም፡፡ ጥሩ ዕረፍት ማድረግ እፈልጋለሁ፡፡ ምክንያቱም በጣም በጣም ደክሞኛል … ሰልችቶኛል፡፡ እውነቴን ነው የምልህ ተረጋግቼ ያለሁበት ሁኔታ ነው፡፡ ምንም ዓይነት ጥላቻ በውስጤ የለም፡፡ ምንም ዓይነት ብስጭት የለኝም፡፡ ምንም ዓይነት መጥፎ ስሜት አይሰማኝም፡፡ በቃ … የመጨረሻ እርጋታና ዕረፍት ውስጥ ነው ያለሁት፤›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ፕ/ር ማሞ ሙጬ ስለ ኢትዮጵያዊነት፣ ስለ ዘር ፖለቲካ፣ ስለ ፓን አፍሪካኒዝም

ፕ/ር ማሞ ሙጬ  ስለ ኢትዮጵያዊነት፣ ስለ ዘር ፖለቲካ፣ ስለ ፓን አፍሪካኒዝም

በተለያዩ ድረ-ገፆች በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሚያንሸራሽሩት ሃሳብ ይታወቃሉ፡፡ ስለ ኢትዮጵያኒዝም፣ ስለ ፓንአፍሪካኒዝም እንቅስቃሴዎች የተለያዩ ምልከታዎችና ምክረ ሃሳቦችን በማቅረብ ተሰሚነት ካላቸው ኢትዮጵያዊያን ምሁራን አንዱ ናቸው – ፕ/ር ማሞ ሙጬ፡፡ ሰሞኑን ጐንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 60ኛ አመት በዓል ሲያከብር  “Towards Innovative Africa: The Significance of Science, Technology, Engineering and Innovation for Sustainable Development” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡

Thursday, July 10, 2014

መንግስታዊ ሽብርተኝነትን የሚሸከም ትከሻ አይኖረንም!!!


ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎችን በማፈንና በማሰቃየት ብሎም በመግደል የአፈና አገዛዙን ለረጅም ጊዜ ሲያራምድ መቆየቱ ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ በተለይም ባለፉት 10 ዓመታት የህዝብን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማፈን እስራትና ግድያውን ህጋዊ ለማስመሰል የተለያዩ አፋኝ አዋጆችን አውጥቷል፡፡ እነዚህን አዋጆችንም ተገን አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባለትን፣ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማት መሪዎችን እና በአገዛዙ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ማሰሩን፣ ማሰቃየቱንና ግድያውን ተያይዞታል፡፡ በህገ መንግስቱ የተካተቱ የሰብዓዊ መብቶችንና ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በሙሉ የሚጥሰውና የአምባገነንነት ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ያፀደቀው የፀረ-ሽብር አዋጅ ከፀደቀበት እለት አንስቶ ኢህአዴግ ለስልጣኔ ያሰጉኛል የሚላቸውን ፍፁም ሰላማዊ ታጋዮችንና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው በድፍረት የፃፉ ጋዜጠኞችን ብሎም የእምነት ነፃነታችን ይከበር ብለው የጠየቁ የሀይማኖት መሪዎችን በጠራራ ፀሃይ ያለምንም ወንጀል በዚሁ ህገ ወጥ አዋጅ ‹‹የፀረ ሽብር ግብረ ሀይል›› በሚባል ማንነቱ በማይታወቅ የጨለማ ቡድን ወደ እስር ቤት እያጋዘ ይገኛል፡፡

ፋሽስታዊ ፕሮፖጋንዳው እና ምላሻችን!


ፋሽስታዊ ፕሮፖጋንዳው እና ምላሻችን!( pdf )

ሐምሌ 3 ቀን 2006 ዓ.ም.
ዘረኛውና ፋሽስታዊ ወያኔ፣ የኢትዮጵያዊያንን የትግል መንፈስ ለመስበር እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ለነፃነትና ለፍትህ የሚያደርገውን ትግል ወኔ ለመስለብ ያቀደበትን የመጀመሪያውን ፕሮፖጋንዳ ለቀቀ። የህግ ልጓም የማያውቀው ፋሽስት በግፍ የያዛቸውን ሰዎችን እይስሙላው ፍርድ ቤት እንኳን ከመቅረባቸው በፊት “ወንጀለኛ” እያለ እንዲህ ዓይነቱ ፕሮፖጋንዳ እንደሚነዛባቸው ተደጋግሞ የታየ በመሆኑ ይህ ፕሮፖጋንዳ የሚጠበቅ ነበር። ሆኖም ግን ፕሮፖጋንዳው ያዘጋጁ ሰዎች ተስፋ ያደረጉትን ውጤት ያመጣ አልሆነም። ወደፊት ደግሞ ሌሎች ሙከራዎች ይደረጉ ይሆናል፤ ውጤታቸው ግን ከዚህኛው የተለየ እንደማይሆን ይገመታል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ከኢቲቪ የእውነት ጥፍጣፊ እንኳን እንደማይገኝ ያውቃል።
በአሁኑ ተቆራርጦ በተለጣጠፈ ፊልም በታጀበው ፕሮፖጋንዳ ውስጥ፣ መሪያችን አንዳርጋቸው ጽጌ በምግብና ውሀ እጦት ብቻ ሳይሆን በተፈጸመበት የተለያዩ የማሰቃያ ወንጀሎች ብዛት አካሉ መዳከሙ ይታያል። ያም ሆኖ ግን ከእሱ ወጥተው እንድንሰማቸው የተደረጉት ቃላት የመንፈሱን ጥንካሬ ገላጮች ናቸው። እሱ ሥራውን መጨረሱንና በዚህም ምክንያት ህሊናው የተረጋጋ መሆኑን ነው የሰማናቸው ቃላት የነገሩን። በዚህ አጭር አጋጣሚ እሱ ግዴታውን ማጠናቀቁ፤ ሀገራችን ከወያኔ ፋስሽቶች ነፃ የማውጣት ኃላፊነቱ በእኛ ትከሻ ላይ መውደቁን ነገረን። ለዜናው ማጀቢያነት የገቡት ፎቶግራፎችም መሪያችን ፈታኝ በሆነ የተፈጥሮ አካባቢ የከፈለውን መስዋዕትነት የሚመሰክሩ ሆነው ተገኙ።

Wednesday, July 9, 2014

በየመን መንግስትና በወያኔ ስርአት ታጋይ አንዳርጋቸው ፅጌ የተወሰደውን ያፈና በመቃወም ከት.ህ.ዴ.ን. የተሰጠ ድርጅታዊ መግለጫ

የወያኔ ኢህአዴግ ስርአት ባለፉት 23 ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል እየፈፀመ መቆየቱና አሁንም እየቀጠለበት መሆኑ ይታወቃል የወያኔ አምባገነን ስርአት ህዝቡን እየጨፈጨፈና ለነፃነት የቆሙትን ቁርጠኛ ታጋዮች በመግደል፣ የህዝቡን የትግል ማእበል መግታት እንደማይቻል ካለፉት አባቶቹ መማር በተገባው ነበር።
ትናንት በወያኔዎች ቀጥተኛ መሪነት ይካሄድ በነበረውና በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ጀግኖች ለጭቁኑ ህዝብ ሲሉ በጠላት ስር የወደቁና ባውደ ውጊያ ፊት ለፊት ተዋግተው መስዋእትነት በመክፈላቸው፣ ህዝባዊ ትግሉ በበለጠ እልህና ቆራጥነት ሲቀጥል እንጂ፣ በከፈለው መስዋእትነት ተደናግጦና ተስፋ ቆርጦ ትግሉ ወደ ኋላ ሲመለስና ትርጉም የለሽ ሲሆን አልታየም።

አንድነት “መንግስት የውንብድና ጥቃት እያደረሰብኝ ነው” አለ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የአዲስ አበባ ም/ቤት ስራ አስፈፃሚዎች፤ ገዢው ፓርቲ በአንድነት አባላት ላይ የመንግስታዊ ውንብድና ጥቃት እያደረሰብን ነው ሲል የከሰሱ ሲሆን ጥቃቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ ጠይቀዋል፡፡
የፓርቲው የአዲስ አበባ ምክር ቤት፤በመንግስት ውንብድና ጥቃት ደርሶባቸዋል ያላቸውን የአመራር አባላት ስም ዝርዝር ይፋ ያደረገ ሲሆን ስማቸው ከተጠቀሰው 13 የፓርቲው አባላት ውስጥ የአንድነት የአዲስ አበባ ስራ አስፈፃሚና ፀሀፊ አቶ እንግዳወርቅ ማሞ፤ በመንግስት ደህንነቶች ደረሰብኝ ያሉትን የአካል ጉዳት አሳይተዋል፡፡ ፀሐፊው የወለቀውን የታችኛው ጥርሳቸውን ለጋዜጠኞች ያሳዩ ሲሆን፣ “ይህ ጥቃት የደረሰብን በጠራራ ፀሐይ በመንግስት ወንበዴዎች ነው” ሲሉ አማረዋል፡፡ “የማላውቃቸው ሰዎች በተደጋጋሚ እየደወሉ ማስጠንቀቂያ ይሰጡኝ ነበር ያሉት” አቶ እንግዳወርቅ፤ ሰኔ 19 ቀን 2006 ዓ.ም በመጀመሪያ በመኪና ሊገጩኝ ሞክረው አልተሳካላቸውም” ካሉ በኋላ፤ ዞረው መጥተው የእኔንና የፓርቲዬን ስም በመጠየቅ መኪና ውስጥ በግድ ሊያስገቡኝ ሞክረው “ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ አልሄድም” በማለቴ፣ በሽጉጥ ሰደፍ በደረሰብኝ ድብደባ ጥርሴ ከመውለቁም ባሻገር፣ መላ ሰውነቴ ተጎድቷል በማለት የወለቀ ጥርሳቸውን አሳይተዋል፡፡

ሶስቱ አምባገነኖች (እየሩሳሌም አርአያ)

አገሪቱ በሶስት ሰዎች ቁጥጥር ስር እንደወደቀችና አሁን እየተካሄደ ያለው የጅምላ እስርና ድብድባ በነዚህ የሕወሐት ባለስልጣናት ትእዛዝ እየተፈፀመ እንደሚገኝ ታማኝ የቅርብ ምንጮች አረጋግጠዋል። የፌዴራል ደህንነት መሪ ፀጋዬ በርሔ (ሃለቃ)፣ የደህንነት ሃላፊ ጌታቸው አሰፋና ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ሲሆኑ፣ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ታፍነው እንዲወሰዱና በዛሬው እለት አብርሃ ደስታን ጨምሮ ሃብታሙ አያሌውና የሺዋስ አሰፋ እንዲሁም ሌሎች የተቃዋሚ አመራር አባላቶች የሃይል ጥቃት እየተፈፀመባቸው እስር ቤት እንዲገቡ ማድረጋቸውን ምንጮቹ ገልፀዋል። አብርሃ ደስታ በፌዴራል ፖሊሶች ተይዞ ሲወሰድ ከፍተኛ ድብደባ የተፈፀመበት ሲሆን በመቀሌ በሚገኙ እስር ቤቶች ውስጥ እንደሌለና ወዴት እንደተወሰደ እንደማይታወቅ ምንጮች ከስፍራው አረጋግጠዋል። ይህ ሁሉ ጥቃትና የመብት ረገጣ እየተከናወነ ያለው በሶስቱ አምባግነኖች መሆኑን ያስታወቁት ምንጮቹ አክለውም እስር፣ ድብደባና ድራማ በመስራት የስልጣን እድሜን ማራዘም አይቻልም ብለዋል። የኢትዮጵያ ነገር ያበቃው በነሃለቃ ፀጋይ በርሄ (ደናቁርት) መመራት የጀመረች እለት ነው- ሲሉ አክለዋል።

Tuesday, July 8, 2014

እኔም አንዳርጋቸው ነኝ! እኔም ግንቦት ሰባት ነኝ!

በአበበ ገላው
የአፓርታይድ ስርአት መገለጫዎች አድልኦ፣ የዘር መከፋፈል፣ ጭቆና፣ ምዝበራ፣ ዝርፊያ፣ የመሬት ንጥቂያ፣ ግድያ፣ እስራት፣ ግርፊያ፣ ሰቆቃ፣…ዋነኞቹ ናቸው። እነዚህም የአፓርታይድ ስርአት መገለጫዎች ከደርግ የከፋው የህወሃቶች ስርወ መንግስት ዋነኛ ባህሪያት መሆናቸው አለም ያወቀው ጸሃይ የሞቀው እውነታ ነው።
abebe.jpgባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ፣ ህወሃት መራሹ ፋሺስታዊ ስርወ መንግስት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በርካታ ዘግናኝ ወንጀሎችን ፈጽሟል። በኦሮሚያ ክልል ገበሬዎች ያለ አግባቡ ከመሬታቸው መፈናቀላቸውን የተቃወሙ ተማሪዎች ላይ ተኩስ በመክፈት በመቶዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች ላይ ግድያና የአካል ጉዳት ፈጽሟል። ከዚህም አልፎ በሺ የሚቆጠሩ ተማሪዎች የጅምላ እስር፣ አፈና፣  ሰቆቃና ከትምህርት ገበታቸው መፈናቀል ገጥሟቸው ህይወታቸው ተመሰቃቅሏል፣ ህልማቸው ጨልሟል።

ሕወሃት በኢትዮጵያ ውስጥ የትግራይ አይሁድ ስርአትን የመዘርጋት ምስጢራዊ እቅድ አለው።

ሕወሃት በኢትዮጵያ ውስጥ የትግራይ አይሁድ ስርአትን የመዘርጋት ምስጢራዊ እቅድ አለው። (ምንጭ‪#‎ምንሊክሳልስዊ‬)
ስብሃት ነጋ ከአሜሪካ መንግስት በወር 10.000 ዶላይ ደምወዝ ይከፈለዋል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በአሁን ወቅት ስብሃት ነጋ የያዘውን ስልጣን የቀድሞው የኢንስቲትዩቱ ፕረዝዳት የነበረው ዶክተር ክንፈ አብርሃ እንደሞተ ወያኔ ዶክተሩን የሚተካ ሰው በማጣቱ በትም ተቸግሮ ስለነበር ቦታውን እንዲይዝ የተፈለገው የትግራይ ተወላጅ ስለነበር አቶ መለስ ዜናዊ በዘር ቆጠራ ሲያጠያይቁ አንድ በሃይለስላሴ ጊዜ ወደ ካናዳ ለትምህርት ሂደው ደርግ ሲመጣ በዛው በጥገኝነት የቀሩ ህይወታቸውን ሙሉ ወርልድ ባንክ የሰሩ እና የተማሩ በጡረታ የሚኖሩ ዲያስፖራ አዛውንት ኢትዮጵያን በዘረኝነት ሳይሆን በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ብቻ የሚያውቛትን ዶክተር የትግራይ ተወላጅ አስጠርቶ ሊሾማቸው አስቦ አልተሳካለም። ለምን ?

Monday, July 7, 2014

የአቶ አንዳርጋቸዉ እገታና የመብት ተሟጋቹ ተቋም

የአዉሮጳ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የመን-ርዕሠ ከተማ ሰነዓ አዉሮፕላን ማረፊያ ተይዘዉ ወደ ኢትዮጵያ ተግዘዋል የተባሉትን የግንቦት ሰባት ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌን ለማስፈታት እንዲጥሩGESELLSCHAFT FÜR BEDROHTE VÖLKER የተሰኘዉ የጀርመን የመብት ተሟጋች ድርጅት ጠየቀ።

Flash-Galerie Airbus A 350 800 XWB
ለተጨቆኑ ሰዎች ጥብቅና የቆመዉ ድርጅት ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ አቶ እንዳርጋቸዉ ፅጌንም ሆኑ ሌሎች ኢትዮጵያ ዉስጥ የታሠሩ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ለማስፈታት የአዉሮጳ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሠብአዊ መብት ምክር ቤት ጣልቃ መግባት አለባቸዉ።

የአሸባሪነት ሕግና እኛ

የአሸባሪነት ሕግና እኛ

terrorism
የግንቦት ሰባቱ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በዚያ ኢትዮጵያዊያኑን በሚበላው ምድርና በሚበሉት አራዊት ከአካላቸው በስተቀር የሰውነት መገለጫ በሌላቸው ማሰብ የሚባል ነገር በማያውቁት ዘገምተኞች እጅ ሲታገትና በኋላም ተላልፎ ተሰጠ ሲባል ይሄንን ድንገተኛ አሳዛኝና ልብ ሠባሪ ዜና የሚገልጹትን ይዞች (ሊንኮች) እንዳየሁት ተጋርቸ (ሼር አድርጌ) በመጽሐፈ ገጼ (በፌስቡኬ) ለጠፍኩት (ፖስት አደረኩት) በማግስቱ አንድ ወዳጀ ምን ይለኛል? ኢትዮጵያ ውስጥ ይሄንን ዜና ፖስት ያደረገ (የለጠፈ) አንተ ብቻ ሳትሆን አትቀርም አለኝ፡፡ አንተስ አላደረከውም? ስል ጠየኩት የለበጣ ፈገግታ እያሳየኝ “አዬ አንተ! ይሄንን ማድረግ በአሸባሪነት ሊያስከስስ እንደሚችል አታውቅም?” ሲለኝ እየቀለደ መስሎኝ ነበር በኋላ ላይ ኮስተር ብሎ “ቆይ! ምን አስበህ ነው? ኢትዮጵያ ውስጥ እየኖርክ እንዴት እንዲህ ታደርጋለህ? በገዛ እጅህ እኮ ገመዳቸው ውስጥ ገባህላቸው” ምንትስ ሲለኝ የምሩን እንደሆነ ገባኝና የትኛው ሕግ ነው ይሄንን የሚለው? ስል ጠየኩት፤ የቻለውን ያህል ይሄ አገዛዝ (ወያኔ) “የአሸባሪነት ሕግ” ሲል ያወጣውን አስቂኝና አስገራሚ ሕግ አስረዳኝ፡፡ ሕጉ ሥራ ላይ እንደዋለም በብዙኃን መገናኛ ተገልጾ እንደነበረ ነግሮኝ እንዴት ግንዛቤው ሳይኖረኝ እንደቀረ ተገርሞ ጠየቀኝ፡፡ ቶሎ ብየም የለጠፍኩትን እንዳጠፋ መከረኝ፡፡

Sunday, July 6, 2014

አዜብ መስፍን በጠና ታመዋል፤ የአባዱላ ገመዳ ልጅ አረፈ – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

azebከባለቤታቸው ህልፈት በኋላ ከፖለቲካው መድረክ እየተገለሉ የመጡት ወ/ሮ አዜብ መስፍን በጠና መታመማቸውን ቅርበት ያላቸው ታማኝ ምንጮች አስታወቁ። በስኳር ህመምና በደም ግፊት እየተሰቃዩ የሚገኙት አዜብ መስፍን የሰውነት ክብደታቸው እንደቀነሰና የመጎሳቆል ሁኔታ በገጽታቸው እንደሚታይ የጠቆሙት ምንጮቹ ለስኳር በሽታ በየእለቱ ከሚወስዱት መድሃኒት በተጨማሪ ለደም ግፊትም እንክብሎችን እንደሚወስዱ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። አዜብ በመኖሪያቸው አብዛኛውን ቀናት እንደሚያሳልፉ የጠቆሙት ምንጮቹ በፖለቲካው የደረሰባቸው ኪሳራ ብስጭት ውስጥ እንደከተታቸውና ለበሽታ እንደዳረጋቸው አያይዘው ገለጸዋል።

ከግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪ

          ከግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ                                                 የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪ
ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን!!!

ሰኔ 29 ቀን 2006 ዓ.ም
በየጊዜው እየከረረና እየገረረ የመጣው ትግላችን “ሁላችን አንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን” ወደ ተባለ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። ይህ ጽሁፍ የዚህን የትግል ምዕራፍ ምንነትና ይዘት በአጭሩ ያብራራል። በዚህ ጽሁፍ ላይ የሰፈሩት ዓረፍተ ነገሮች ተነበው የሚታለፉ ሳይሆን በተግባር የሚተረጎሙ ሥራዎች ናቸው።
አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ምን ማለት ነው? አንዳርጋቸው ጽጌ ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲና ለእኩልነት በጀግንነት የቆመ፤ ትግሉ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት ሁሉ ሲከፍል የነበረና አሁንም እየከፈለ ያለ መሪያችን ነው። አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት ልክ እንደሱ ትሁት ሆኖም ግን ቆራጥ፤ ሆደ ሰፊ በዚያው ልክ ደግሞ መራር፤ አስተዋይና ብልህ ሆኖም ተግባር ተኮር መሆን ማለት ነው። አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት ወያኔን ለማስወገድ መደረግ የሚገባውን እርምጃ ለመውሰድ የተዘጋጀ ሰው መሆን ማለት ነው። አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት ለአገርና ለትውልድ ቤዛ መሆን ማለት ነው።
ወያኔ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ ካተኮረባቸው ምክንያቶች አንዱ የወያኔን የዘር ፓለቲካና ፕሮፖጋንዳ በሚያመክን መልኩ በተግባር ትግል ውስጥ ካሉ የኦሮሞ፣ የአፋር፣ የኦጋዴን፣ የጋምቤላ እና ሌሎች ዘውግ ተኮር ድርጅቶች ጋር ንቅናቄዓችን ተግባራዊ ትብብር ማድረግ የሚችሉበት ደረጃ ድረስ ማቀራረብ የቻለ መሪ መሆኑ ነው። ከሁሉም በላይ ለወያኔ የጉሮሮ ቁስል የሆነበት ደግሞ ከትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) ጋር ግንቦት 7 የፈጠረው ጠንካራ ትብብር ነው። ከትህዴን ጋር በመሆን አቶ አንዳርጋቸው ወያኔ በትግራይ ሕዝብ ጀርባ መንጠልጠል እንዳይችል አድርጎታል። እናም አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት ከዘረኝነት ፀድቶ መገኘት ማለትም ጭምር ነው። አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት በኢትዮጵያዊያን እኩልነት እና እኩል ባለመብትነት ከልብ ማመን እና ለእኩልነት በጽናት መታገል ማለት ነው።

Friday, July 4, 2014

የመን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለወያኔ ፋሽስቶች አሳልፋ መስጠቷን በማስመልከት የወጣ መግለጫ


የመን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለወያኔ ፋሽስቶች አሳልፋ መስጠቷን በማስመልከት የወጣ መግለጫ
ሰኔ 27 ቀን 2006 ዓ.ም
የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቶ መቆየቱ ማስታወቃችን ይታወሳል።
የየመን መንግሥት በህገወጥ መንገድ ያገተብንን የንቅናቄዓችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። የአገሩን የረዥም ጊዜ ጥቅም ማየት የተሳነው የየመን መንግሥት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ይልቅ አምባገኑን ወያኔ መርጦ መሪያችንን ለእርድ አሳልፎ ሰጥቶብናል። በዚህም ሳቢያ የየመን መንግሥት ይቅርታ የማያሰጥ፤ ዘመን የማይሽረው ታሪካዊ ስህተት ፈጽሟል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ለወዳጅ ጎረቤት ትሁትና ቀና ቢሆንም ጥቃት በሚያደርስበት የቅርብም ሆነ የሩቅ ጎረቤት ላይ ግን ቁጣውን የሚመጥን የአፀፋ እርምጃ መውሰድ ያውቅበታል።